Saturday, 04 July 2015 11:37

በብሩንዲ ምርጫን ተከትሎ በተነሳ ግጭት 6 ሰዎች ሞቱ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

አወዛጋቢው የብሩንዲ ምርጫ ባለፈው ሰኞ መካሄዱን ተከትሎ ባለፈው ረቡዕ በመዲናዋ ቡጁምቡራ በተቀሰቀሰ ግጭት አንድ የፖሊስ መኮንንን ጨምሮ ስድስት ሰዎች ለህልፈተ ህይወት መዳረጋቸውን ቻናል አፍሪካ ዘገበ፡፡
የአገሪቱ ፕሬዚዳንት ፔሪ ንኩሩንዚዛ ህገ መንግስቱ ከሚፈቅድላቸው ውጪ ለሶስተኛ ዙር በምርጫ ለመወዳደር መወሰናቸውን የተቃወሙ ዜጎች ለወራት የዘለቀ ግጭት ሲፈጥሩ የቆዩ ሲሆን፣ የምርጫ ውጤቱ ይፋ ይደረጋል ተብሎ በሚጠበቅበት ባለፈው ረቡዕም ከፖሊስ ጋር መጋጨታቸውን ዘገባው ገልጧል፡፡
17 ያህል የአገሪቱ ተቃዋሚ ፓርቲዎች ራሳቸውን ባገለሉበት የሰኞው ምርጫ ድምጽ ለመስጠት የተመዘገበው ህዝብ ብዛት 3.8 ሚሊዮን እንደነበር የጠቆመው ዘገባው፣ ይህም ሆኖ በመዲናዋ ቡጁምቡራና በአካባቢዋ ድምጹን የሰጠው ህዝብ ቁጥር አነስተኛ ነበር ብሏል፡፡ የምርጫው ድምጽ ቆጠራ ባለፈው ማክሰኞ መጠናቀቁን የአገሪቱ የምርጫ ኮሚሽን አስታውቋል፡፡
ለወራት በዘለቀው ግጭት ከ70 በላይ የአገሪቱ ዜጎች ለህልፈተ ህይወት መዳረጋቸውንም ዘገባው አስታውሷል፡፡

Read 1306 times