Saturday, 11 July 2015 10:46

በመዲናዋ ታላቅ የችግኝ ተከላ ይካሄዳል

Written by 
Rate this item
(0 votes)

  ዛሬ በአቡነ ጴጥሮስ አደባባይ ይጀመራል
   የክረምቱን መግባት ተከትሎ በመዲናዋ ታላቅ የችግኝ ተከላ ፕሮግራም ዘመቻ አርሴማ በሚል የተዘጋጀ ሲሆን ዛሬ በአቡነ ጴጥሮስ አደባባይ አካባቢ ተከላው ይጀመራል፡፡  
 ወደ 150 ሰው ገደማ ይሳተፍበታል ተብሎ በሚጠበቀው የችግኝ ተከላ ፕሮግራም፤ከአቡነ ጴጥሮስ እስከ ፖሊስ ክበብ ባለው የዋናው መንገድ አካፋይ ላይ ወደ 280 የተለያዩ የዛፍ ዝርያዎች እንደሚተከሉ ፕሮጀክቱን የሚመራው ኤልፍሬዝ ፕሬስ ስራዎች ኃላ.የተ.የግ. ማህበር አስታውቋል፡፡
የችግኝ ተከላ አስተባባሪዋ አርሴማ በቀለ፤ከዛሬው ፕሮግራም በተጨማሪ ከሐምሌ 4-9  ለ 5 ቀናት የሚዘልቅ ታላቅ የችግኝ ተከላ ፕሮግራም በመዲናይቱ መዘጋጀቱን ለአዲስ አድማስ ገልጻለች፡፡  የችግኝ ተከላው ሐምሌ 4 በሚኪላንድ አካባቢ የሚጀመር ሲሆን በሌሎች በተመረጡ አካባቢዎችም ይከናወናል ተብሏል፡፡
የችግኝ ተከላው የሚካሄደው በበጐ ፍቃደኛ ወጣቶችና የህብረተሰቡ ክፍሎች መሆኑን የጠቆመችው አስተባባሪዋ፤የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ችግኞችን በጉዲፈቻ (በአደራ) እንደሚሠጥና ተካዩ አመቱን ሙሉ የመንከባከብ ግዴታ እንደሚጣልበት ተናግራለች፡፡  
የአካባቢ መራቆት በአሳሳቢ ሁኔታ ላይ እንደሚገኝ የገለጸችው አስተባባሪዋ፤ድርጅቷ እየጠፋ ያለውን የደን ሃብት የመታደግ አላማ አንግቦ መርሃግብሩን ለማከናወን እንዳቀደ ገልፃለች፡፡ በየአመቱም የችግኝ ተከላና እንክብካቤ በመዲናዋና ከመዲናዋ ውጪም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የፕሮጀክቱ አስተባባሪ ገልፃለች፡፡
ኤልፋሬዝ ፕሬስ ስራዎች “አርሴማ” የተሰኘች ጋዜጣ የሚያሣትም ሲሆን ላለፉት 7 አመታት በማህበራዊና በሴቶች ጉዳይ ላይ አተኩራ ስትታተም ቆይታለች፡፡

Read 1868 times