Saturday, 18 July 2015 10:14

ኢትዮጵያ ዘንድሮ ከግመል ወተት ከ 6 ሚ.ብር በላይ ገቢ ታገኛለች

Written by  አለማየሁ አንበሴ
Rate this item
(0 votes)

ኢትዮጵያ የግመል ወተት ወደ ውጭ በመላክ እየተገባደደ ባለው የበጀት ዓመት ከ6 ሚሊዮን ብር በላይ እንደምታገኝ የስጋና ወተት ልማት ኢንስቲትዩት መረጃ ጠቆመ፡፡ የግመል ወተት ወደ ውጪ ቢላክ ከፍተኛ ጥቅም እንደሚያስገኝ ተገንዝባ ዘንድሮ ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ 3 የምስራቅ አፍሪካ ሃገራት በመላክ ገቢ ማግኘቷም ታውቋል፡፡ ሃገሪቱ ዘንድሮ ለፑንትላንድ፣ ሶማሌ ላንድና ጅቡቲ የግመል ወተት የላከች ሲሆን እነዚህ አገሮችም የኢትዮጵያን የግመል ወተት ወደውት ለመሸመት ፍላጎት አሳይተዋል ተብሏል፡፡
በአሁን ሰዓት አንድ ግመል እስከ 6 ሊትር ወተት በቀን የምትሰጥ ሲሆን የአንድ ሊትር ዋጋ ከ400 ብር በላይ እንደሆነ ተገልጿል፡፡ ሃገሪቱ ወደፊት የግመል ሃብቷን በአግባቡ ከተጠቀመች፤ ከግመል ወተት ከፍተኛ ገቢ ልታገኝ እንደምትችል ኢንስቲትዩቱ ተንብየዋል፡፡

Read 2795 times