Monday, 27 July 2015 11:01

3ሺ የናይሮቢ የጎዳና ተዳዳሪዎች ተሃድሶ ገቡ! የእኛዎቹስ?

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

 “ከልጅ ልጅ ቢለዩ…”
የኦባማ ጉብኝት ኬንያንና ኢትዮጵያን ከምንጊዜውም በላይ ቁጭ ብድግ እንዳሰኛቸው እያየን ነው፡፡ የኬንያ ጋዜጦች እንደዘገቡት፤ ናይሮቢን ጨምሮ ፕሬዚዳንቱ ይጎበኙዋቸዋል የተባሉ ከተሞች ሁሉ ሲታጠቡና ሲቀባቡ ነው የሰነበቱት፡፡ በናይሮቢ ጐዳና የኦባማ ትልቅ ምስል ተሰቅሎ ይታያል፡፡የአሜሪካ የፀጥታና ደህንነት ሃይል ኬንያን የመፈተሽና ከሽብር ጥቃት ነፃ የማድረግ እንቅስቃሴ የጀመረው ከሁለት ሳምንት በፊት ነው፡፡ 8 ሄሊኮፕተሮች ከኦባማ ቀድመው ኬንያ መግባታቸው ይታወቃል፡፡ በነገራችን ላይ… ከተማም… ገፅታም… ፀጥታም ያበላሻሉ ተብለው የታሰቡ… ከ3ሺ በላይ የናይሮቢ የጎዳና ተዳዳሪዎች ተሰብስበው የአንደኛ ደረጃ ት/ቤት ግቢ ውስጥ እንደከተሙ ዘ ስታንዳርድ ጋዜጣ ዘግቧል፡፡ ከጐዳና ተዳዳሪዎቹ ውስጥ ቢያንስ ግማሾቹ ዕድሜያቸው ከ18 ዓመት በታች ነው ተብሏል፡፡ የማን ሃሳብ ወይም እቅድ እንደሆነ ባይታወቅም ከ3ሺ በላይ እንደሚሆኑ የተገመቱት የጎዳና ተዳዳሪዎች ት/ቤቱ ውስጥ ተከርችመው አይቀመጡም፡፡ ጊዜያዊ የተሃድሶ ማዕከል እንደሚገቡ ተነግሯል፡፡ የናይሮቢ ከተማ ገዢ ኢቫንስ ኪዴሮ ስለ ፕሮጀክቱ ሲናገሩ፤ “የተሃድሶ ፕሮግራሙ የምግብ፣ የልብስና የመጠለያ አቅርቦትን ይጨምራል፡፡ በጐዳና ላይ ከለመዱት የተሻለ ምቾት ያገኛሉ” ብለዋል፡፡ የናይሮቢ ከተማ መስተዳድር ሰዎቹን ከጎዳና ላይ ሰብስቦ ለማንሳት 40ሚ. የኬንያ ሽልንግ መቀበሉን ኪዴሮ ገልፀዋል፡፡ የገንዘቡ ምንጭ ባይጠቀስም ከኦባማ መንግስት ሊሆን እንደሚችል ተገምቷል፡፡ በተሃድሶው ፕሮግራም የጎዳና ተዳዳሪዎቹን ከእነአካቴው ከጐዳና ህይወት የማላቀቅ ዘላቂ ዕቅድ ይኑር አይኑር አልታወቀም፡፡ ቢሆንላቸውማ በማን ዕድላቸው! “የራሷ አሮባት የሰው ታማስላለች…” ብትሉኝ አመሰግናችሁ ነበር፡፡ ለመሆኑ የእኛስ የጐዳና ተዳዳሪዎች የት ገቡ? ኦባማ መቼም አይረሷቸውም ብለን ተስፋ እናደርጋለን፡፡ “ከልጅ ልጅ ቢለዩ…” ነው ነገሩ፡፡

Read 2679 times