Monday, 27 July 2015 11:06

ኦባማና የምስራቅ አፍሪካ ጉብኝታቸው

Written by 
Rate this item
(7 votes)

 አስደማሚ … አስገራሚ … አስደናቂ እውነታዎች!?
          የኬንያው ጠንቋይ፤ “ኦባማ የአባቱን አገር ይጎበኛል” ሲል ተነበየ
             “የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ይሆናሉ ብሎ ተንብዮ ነበር” (USA Today)
   ባራክ ኦባማ በፕሮግራም መጣበብ የተነሳ በኬንያ ቆይታቸው የአባታቸውን የትውልድ ሥፍራ (ኮጌሎ) ለመጎብኘት እንደማይችሉ እየተነገረ ቢሆንም ዕውቅ አንድ የኬንያ ጠንቋይ ፕሬዚዳንቱ የአያት ቅድመ አያቶቻቸውን አገር ይጎበኛሉ ሲል ሰሞኑን ተንብየዋል፡፡
ጆን ዲሞ የተባለው የኮጌሎ ጠንቋይ፤ ኦባማ በእርግጠኝነት የአባታቸውን የትውልድ ቀዬ እንደሚጎበኙ ታይቶኛል ብሏል፡፡ ኦባማ እስካሁን ኮጌሎን እንደሚጎበኙ ማረጋገጫ ባይሰጡም የመንደሩ ነዋሪዎች ግን አሁንም በተስፋ እየጠበቁ ነው፡፡ ስለዚህም ምናልባት ከመጡ በሚል ዝግጅታቸውን ቀጥለዋል፡፡
“እመኑኝ … ኦባማ የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ይሆናል ብዬ ነበር፤ ሆነ፡፡ አሁንም የወላጆቹን የትውልድ ቀዬ የመጎብኘት ዕቅድ እንዳለው ታይቶኛል፡፡ ይመጣል፡፡” ሲል ተንብየዋል ዲሞ፡፡ ጆን ዲሞ እ.ኤ.አ በ2006 ዓ.ም ኦባማ ፕሬዚዳንት ይሆናሉ ብሎ መተንበዩን “ዩኤስኤ ቱዴይ” አስታውሷል፡፡ “ውጤቱ ኦባማ ኮጌሎ እንደሚመጣ ነው የሚጠቁመው፡፡ ይሄ ትልቅ ምስጢር ነው፡፡ የቅድመ አያቱን አገር እንደሚጎበኝ ለማንም መንገር የለበትም!” በማለት ጠንቋዩ በጉጉት ለተሞሉት የመንደሯ ነዋሪዎች ተናግሯል፡፡ ኦባማ በትላንትናው ዕለት ኬንያ የገቡ ሲሆን የሦስት ቀናት ጉብኝት ያደርጋሉ፡፡ በምዕራባዊ ኬንያ የሚገኘው የኮጌሎ መንደር፤ የአያቱ የሳራ ኦባማ የትውልድ ሥፍራ ሲሆን የአባቱ የባራክ ኦባማ (ሰር) የቀብር ስፍራም ያለው እዚያው ነው፡፡
           

Read 4579 times