የአንጋፋው ደራሲ አበራ ለማ “ቅንጣት - የኔዎቹ ኖቭሌቶች” የተሰኘ አዲስ የልብወለድ መፅሃፍ ሰሞኑን ለገበያ ቀረበ፡፡ በ264 ገፆች የተመጠነው መፅሃፉ፤ በ70 ብር እንደሚሸጥ ታውቋል፡፡
ነዋሪነቱን በኖርዌይ ያደረገው ደራሲው፤ በበርካታ የአጫጭር ልቦለድና የግጥም መድበሎቹ የሚታወቅ ሲሆን ከቀደምት ሥራዎቹ መካከል፡- “ኩል ወይም ጥላሸት” (የግጥም መድበል)፣ “ሸበቶ” (የግጥም መድበል)፣ “ሕይወትና ሞት” (የአጫጭር ልቦለዶች መድበል)፣ “ሞገደኛው ነውጤ” (ኖቭሌት) እና ሌሎችም ይገኙበታል፡፡
በ1980ዎቹ የኢትዮጵያ ደራስያን ማህበር ዋና ፀሃፊ ሆኖ ያገለገለው አበራ ለማ፤ በአሁኑ ሰዓት በኖርዌይ ደራስያን ማህበር የመጀመርያውና ብቸኛው ጥቁር እንዲሁም በአፍ መፍቻው ቋንቋ የሚፅፍ አባል ደራሲ ነው ተብሏል፡፡
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና