Saturday, 01 August 2015 14:51

ፕሬዚዳንት ፑቲን ሴፕ ብላተር የኖቤል ሽልማት ይገባቸዋል አሉ

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

  የሩስያው ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን በሙስና ቅሌት እየታመሰ የሚገኘውን አለማቀፉን የእግር ኳስ ፌዴሬሽን ፊፋ ለረጅም አመታት በፕሬዚዳንት የመሩት ሴፕ ብላተር፣ የዓለም የኖቤል ሽልማት ሊሰጣቸው የሚገባ ታላቅ ሰው ናቸው ሲሉ መናገራቸውን ዘሂንዱ ታይምስ ዘገበ፡፡
ፕሬዚዳንት ፑቲን ባለፈው ሰኞ ከስዊዝ ቲቪ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ፣ ሃሜት የበዛባቸው የፊፋው ፕሬዚዳንት ሴፕ ብላተር ለአለማችን እግር ኳስ ባበረከቱት አስተዋጽኦ የኖቤል ሽልማት ሊሰጣቸው የሚገባ ታላቅ ሰው ናቸው ብለዋል፡፡  እንደ ብላተር ያሉ ትጉሃን ሰዎች፣ የተሰጣቸውን ሃላፊነት በአግባቡ በመወጣት ላበረከቱት አስተዋጽኦ ልዩ እውቅና ሊሰጣቸው ይገባል ሲሉም አክለዋል ፕሬዚዳንት ፑቲን፡፡ ብላተር በበኩላቸው፤ የፑቲን ንግግር እንዳስደሰታቸውና ስሜታቸውን እንዳነቃቃው ገልጸው፣ ለፑቲን ምስጋናቸውን አቅርበዋል፡፡ ፑቲንና ብላተር የ2018 የአለም የእግር ኳስ ዋንጫን አዘጋጅ አገር ለመምረጥ ባለፈው ሳምንት መጨረሻ በሩስያ ሴንት ፒተርስበርግ በሚገኘው ኮንስታንቲን ቤተ-መንግስት በተደረገው የመጀመሪያ ዙር እጣ አወጣጥ ስነ-ስርአት ላይ ተገናኝተው እርስ በርስ መወዳደሳቸውን ዘገባው አክሎ ገልጧል፡፡

Read 1687 times