Saturday, 15 August 2015 15:54

የግሪክ ኢኮኖሚ ያልተጠበቀ እድገት ማሳየቱ ተነገረ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

በእዳ ጫና አስከፊ ቀውስ ውስጥ ገብቶ የከረመው የግሪክ ኢኮኖሚ በዘንድሮው ሁለተኛ ሩብ አመት የዜሮ ነጥብ ስምንት በመቶ ያልተጠበቀ እድገት ማሳየቱን ቢቢሲ ዘገበ፡፡
የአገሪቱ ብሄራዊ ስታቲስቲክስ ኤጀንሲ ያወጣውን መረጃ ጠቅሶ ዘገባው እንዳለው፣በዚህ አመት ከ2.1 በመቶ እስከ 2.3 በመቶ ገደማ ይቀንሳል ተብሎ የተገመተው የግሪክ ኢኮኖሚ ባልተጠበቀ ሁኔታ በሁለተኛው ሩብ አመት የ0.8 በመቶ እድገት አስመዝግቧል፡፡
በግሪክ ብሄራዊ ባንክ የኢኮኖሚ ባለሙያ የሆኑት ኒኮስ ማጊናስ እንደገለጹት፤ በሁለተኛው ሩብ አመት የተመዘገበው የኢኮኖሚ እድገት፣ ቀደም ብሎ የተተነበየውን የኢኮኖሚ ውድቀት ከ2 በመቶ በታች ማድረስ እንደሚቻል ያመላከተ ሲሆን ካለፈው አመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸርም የ1.4 በመቶ እድገት አሳይቷል፡፡
ላልተጠበቀው የኢኮኖሚ እድገት አስተዋጽኦ ካበረከቱት ዘርፎች መካከል የፍጆታ፣ የኢንዱስትሪ ምርትና የቱሪዝም መስኮች መነቃቃት ማሳየታቸው እንደሚገኝበት የጠቆሙት ማጊናስ፣ ኢኮኖሚው በመጀመሪያው ሩብ አመት እድገትም ሆነ ውድቀት አለማስመዝገቡን አስታውሰዋል፡፡
የግሪክ አጠቃላይ አገራዊ ምርት ካለፈው ሚያዝያ ወር እስከ ሰኔ ወር ባለው ጊዜ ውስጥ የ0.8 በመቶ እድገት ማሳየቱንም ሮይተርስ ዘግቧል፡፡

Read 1631 times