Saturday, 15 August 2015 16:05

የሜዳልያ ትንበያ

Written by  ግሩም ሠይፉ
Rate this item
(0 votes)

 በአሜሪካው የትራክ ኤንድ ፊልድ አትሌቲክስ መፅሄት ድረገፅ ለ15ኛው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ከመካከለኛ ርቀት እስከ ማራቶን ባሉ የውድድር መደቦች በወቅታዊ ብቃት ላይ ተመስርቶ የሜዳልያ ትንበያ ተሰርቷል። በዚሁ የትራክ ኤንድ ፊልድ ድረገፅ ኤክስፐርቶች ትንበያ ኢትዮጵያ ከፍተኛ ስኬት እንደሚኖራት የተገመተው ከወንዶች ይልቅ በሴቶች አትሌቶች ነው፡፡ በሴቶች ሶስት የወርቅ ፤ 3 የብር እና 2 የነሐስ ሜዳልያዎች ኢትዮጵያ እንድመታስተመዘግብ በትራክ ኤንድ ፊልድ ሲተነበይ በወንዶች ደግሞ በ5ሺ ሜትር ዮሚፍ ቀጀልቻ ብቻ የነሐስ ሜዳልያ እንደሚወስድ ተገልጿል፡፡ በሴቶች ለኢትዮጵያ ከተመዘገቡት 3 የወርቅ ሜዳልያዎች ሁለቱን በ1500 እና በ5000 ሜትር ታስመዘግባለች የተባለው ገንዘቤ ዲባባ ስትሆን 3ኛውን የወርቅ ሜዳልያ በማራቶን ትእግስት ቱፋ ትወስዳለች ተብሏል። ከሶስቱ የብር ሜዳልያ ግምቶች ደግሞ ገለቴ ቡርቃ በ10ሺ ሜትር፤ አልማዝ አያና በ5ሺ ሜትር እንዲሁም ማሬ ዲባባ በማራቶን ሲጠቆሙ፤ ቀሪዎቹን ሁለት የነሐስ ሜዳልያዎች በ3ሺ መሰናክል ህይወት አያሌው እንዲሁም በ10ሺ ሜትር አለሚቱ ሃሮዬ እንደሚያገኙ ተተንብዮላቸዋል፡፡
ከዓለም ሻምፒዮና 1 ወር በፊት የትራክ ኤንድ ፊልድ የወርቅ፤ የብርና የነሐስ ሜዳልያዎች ትንበያ ከመካከለኛ ርቀት እስከ ማራቶን
በወንዶች
በ800 ሜትር
ኒጀል አሞስ ቦትስዋና፤ ዴቪድ ሩዲሻ ከኬንያ፤ አቤል ቱካ ከሰርቢያ
በ1500 ሜትር
አዝቤል ኪፕሮፕ ከኬንያ፤ ሲላስ ኪፕላጋት ከኬንያ፤ አያልነህ ሱሌማን ከጅቡቲ
በ3ሺ መሰናክል
ጃሩስ ቢርዬች ከኬንያ፤ ኢቫን ጃገር ከአሜሪካ ፤ ኮንሴሌስ ኪፕሮቶ ከኬንያ
በ5ሺሜትር
ሞ ፋራህ ከታላቋ ብሪታኒያ፤ ካሌብ ኒዱኩ ኬንያ፤ ዮሚፍ ቀጀልቻ ከኢትዮጵያ
በ10ሺሜትር
ሞ ፋራህ ከብሪታኒያ፤ ጄይሪር ኪፕውሁር ከኬንያ፤ ጋሌን ሩፕ ከአሜሪካ
በማራቶን
ዊልሰን ኪፕሳንግ ከኬንያ፤ ስቴፈን ኪፕሮቺች ከኬንያ፤ ዴኒስ ኪሜቶ ከኬንያ
በሴቶች
በ800 ሜትር
ኢዪንሴ ሰም ከኬንያ፤ አጄል ዊልሰን ከአሜሪካ፤ ጃኔት ኪፕሶጌ ከኬንያ
በ1500 ሜትር
ገንዘቤ ዲባባ ከኬንያ፤ ሰይፋን ሃሰን ከሆላንደ፤ ጄኒ ሲምፕሰን ከአሜሪካ
በ3ሺ መሰናክል
ሃቢባ ጋሪቢ ከቱኒዝያ፤ ቨርጂና ናያምቡራ ከኬንያ፤ ሂይወት አያሌው ከኢትዮጵያከኢትዮጵያ
በ5ሺ ሜትር
ገንዘቤ ዲባባ፤ አልማዝ አያና ከኢትዮጵያ፤ሜርሲ ቼሮኖ ከኬንያ
በ10ሺ ሜትር
ቪቪያን ቼሮይት ከኬንያ፤ ገለቴ ቡርቃ  ከኢትዮጵያ፤ አለሚቱ ሃሮዬ ከኬንያ
በማራቶን
ትግስት ቱፋ ከኢትዮጵያ፤ ማሬ ዲባባ ከኢትዮጵያ፤ ኤድና ኪፕላጋት ከኬንያ

Read 1879 times