ባለፈው ሳምንት ለገበያ የቀረበው ሌላው መፅሐፍ በደራሲ ተስፋዬ ገብረሥላሴ የተደረሰው “ጣፊናስ” የተሰኘ ልብወለድ ነው፡፡ አሁን በህይወት የሌለው ደራሲና ሃያሲ መስፍን ኃብተማርያም በመጽሐፉ የጀርባ ሽፋን ላይ በሰጠው አስተያየት፤ “…በታሪኩ ሂደት ለጥቅም የቆሙና ከአገርና ከህዝብ እንቅደም ያሉ ኢትዮጵያውያን የመኖራቸውን ያህል ለአገራቸው የሚሟገቱና መስዋዕትነት ለመክፈል የቆረጡ ውድ የኢትዮጵያ ልጆችም ስሜትን ወጥረው ይይዛሉ…” ብሏል፡፡ የቅድስት ማርያም ዩኒቨርሲቲ ፕሬስ ያሳተመው “ጣፊናስ”፤ 308 ገፆች ያሉት ሲሆን ዋጋው 68 ብር ነው፡፡
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና