Monday, 31 August 2015 08:46

ህፃናት ተማሪዎችን እርዳታ መለመኛ አድርጓል የተባለው ት/ቤት ታገደ

Written by  አለማየሁ አንበሴ
Rate this item
(2 votes)

     ወርሃ  ዊ ክፍያ  እያስከፈለ የሚያስተምራቸውን ህፃናት ተማሪዎች ከውጭ አገር የገንዘብ እርዳታ መለመኛ አድርጓቸዋል የተባለው ኮቢ አካዳሚ አገልግሎት እንዳይሰጥ ታገደ፡፡
ትምህርት ቤቱ ከወላጆች በወር እስከ 600 ብር እየተቀበለ የሚያስተምራቸውን ህፃናት ተማሪዎች ፎቶግራፍ ለዚሁ ተግባር በተከፈተው ድረ ገፁ ላይ ከአጫጭር መግለጫዎች ጋር በመለጠፍ ወላጆች ሳያውቁ ለልመና ተግባር ሲጠቀምባቸው እንደቆየ ባለፈው ሰኔ 20 ቀን 2007 ዓ.ም በወጣው አዲስ አድማስ ጋዜጣ መዘገቡ ይታወሳል፡፡
ወላጆችም ጉዳዩን ለአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ የቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ 2 ትምህርት ፅ/ቤት ማመልከታቸው አይዘነጋም፡፡
የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮውም ሰሞኑን እንደገለፀው፤ ትምህርት ቤቱን ከመማር ማስተማር ስራው ያገደው ሲሆን በህግም ለመጠየቅ መዘጋጀቱ ታውቋል፡፡
የት/ቤቱ የቀድሞ ዳይሬክተር ከጉዳዩ ጋር በተያያዘ ሥራቸውን በገዛ ፈቃዳቸው እንደለቀቁ ለማወቅ ተችሏል፡፡

Read 2315 times