መርዛማ የሃሞት ፈሳሾች በጉበታችን ላይ ከፍተኛ ጉዳት እንደሚያስከትሉና የጉበት ሴሎችን ቀስ በቀስ ወደ ቲሹዎች በመቀየር ከጥቅም ውጪ ሊያደርጉት እንደሚችሉ ተጠቆመ፡፡
በሔድልበርና ዩኒቨርሲቲ ተመራማሪዎች የተደረገውና በቅርቡ ይፋ የሆነው አንድ ጥናት እንደሚያመለክተው፤ ሃሞት የጉበት ሴሎች ጋር እንዳይደርስ የሚከላከሉት አካላት ሲጠፉና መርዛማ የሃሞት ፈሳሾች የጉበት ሴሎች ጋር ደርሰው ጉዳት ሲያስከትሉ ጉበት Cirrhosis (ኪሮሲስ) ተብሎ ለሚጠራው የጉበት በሽታ ይጋለጣል፡፡ ይህ በሽታ ደግሞ ጉበታችን ተግባሩን በአግባቡ እንዳያከናውን እንቅፋት በመሆንና ሴሎቹን ወደ ቲሹዎች በመቀየር ጉበትን ሙሉ በሙሉ ከጥቅም ውጪ የሚያደርግ መሆኑን ጥናቱ አመልክቷል፡፡
ለዚህ ችግር መነሻ ምክንያቶች ሊሆኑ ይችላሉ ተብሎ በጥናቱ ላይ ከተገለፁት መካከልም የጉበት ቫይረሶች፣ ከፍተኛ የአልኮል መጠጥ፣ መድሃኒቶችና ልዩ ልዩ ኬሚካሎች እንደሚገኙበት ተጠቁሟል፡፡