Saturday, 05 September 2015 10:29

ጆሃንስበርግ በሚሊየነሮች ብዛት ከአፍሪካ ከተሞች ቀዳሚ ሆናለች

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

 ጆሃንስበርግ 23‚400፣ ካይሮ 10‚200፣ ሌጎስ 9‚100 ሚሊየነሮች አሏቸው
            አፍሪካ በድምሩ 670 ቢ. ዶላር ሃብት ያካበቱ 163 ሺህ ሚሊየነሮች አሏት

   የደቡብ አፍሪካዋ ጆሃንስበርግ በአፍሪካ አህጉር በርካታ ሚሊየነሮች የሚገኙባት ቀዳሚ ከተማ መሆኗን አፍርኤዥያ ባንክ እና ኒው ወርልድ ዌልዝ የተሰኙ ተቋማት ሰሞኑን ይፋ ያደረጉትን አህጉራዊ የጥናት ውጤት ጠቅሶ ቢቢሲ ዘገበ፡፡ “የወርቅ ከተማ” ተብላ የምትጠራው ጆሃንስበርግ፤ 23 ሺህ 400 ሚሊየነሮች የሚኖሩባት የአፍሪካ የባለጸጎች ከተማ መሆኗን የገለጸው ዘገባው፣ ደቡብ አፍሪካ በአህጉሩ ከሚገኙ ሚሊየነሮች 30 በመቶው የሚገኙባት አገር መሆኗንም አስታውቋል፡፡
10 ሺህ 200 ሚሊየነሮች ያሏት የግብጽ መዲና ካይሮ፤ በሚሊየነሮች ብዛት ከአህጉሩ ከተሞች ሁለተኛ ደረጃን የያዘች ሲሆን 9 ሺህ 100 ሚሊየነሮች ያሏት የናይጀሪያዋ ሌጎስ ደግሞ ሶስተኛ ደረጃን ይዛለች፡፡
ባለሃብቶቹ በዝርዝሩ ውስጥ ለመካተት ቢያንስ 1 ሚሊዮን ዶላር የተጣራ ሃብት ሊኖራቸው እንደሚገባ የጠቆመው ዘገባው፣ አፍሪካ በድምሩ 670 ቢሊዮን ዶላር ሃብት ያካበቱ 163 ሺህ ሚሊየነሮች እንዳሏትም አክሎ ገልጿል፡፡

Read 2342 times