Friday, 11 September 2015 09:42

“መንግሥት የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ከፈታልን ውጤታማ እንሆናለን” አትሌት ኃይሌ ገ/ሥላሴ

Written by  ግሩም ሠይፉ
Rate this item
(2 votes)

     2007 ራሴን ከውድድር ያገለልኩበት ዓመት ነው፡፡ በርካታ ስራዎችን እየሰራሁ ነው፡፡ በግብርና፣ በሆቴል፣ በተለያዩ ግንባታዎች ላይ ነን፡፡ በተለይ ግብርናችን ጥሩ ሁኔታ ላይ ነው፡፡ የቡና ተክላችን 600 ሄክታር ደርሷል፡፡ የማር ምርት ጨርሰን በ2008 ወደ ገበያ እንገባለን፡፡ ለአገር ውስጥም ለውጪም ገበያ ይቀርባል፡፡ የወርቅ ማእድን ስራዎችም ጀምረናል፡፡
የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ላይ ያስመዘገብነውን ውጤት በተመለከተም እንደ ተመልካች አልቀበለውም፡፡ አንድ ወገንን ለመውቀስ አይደለም፤ አትሌቱም የስፖርት ቤተሰቡም የራሱ ድርሻ አለው፡፡ መንግስት ይኼን ጉዳይ አልባት ካልሰጠው ከብራዚል ስንመለስ የባሰ ነገር ገጥሞን ሁላችንም እንዳናዝን እሰጋለሁ፡፡ ከዚህ በላይ ብዙ ለማለት አልፈልግም፡፡
አዲሱ ዓመት ጥሩ ይሆናል ብዬ እገምታለሁ፡፡ በተሰማራንባቸው ስራዎች እኛንም ተጠቅመን አገርንም ለመጥቀም እንስራለን፡፡ በዋናነት ግን መንግስት መልካም አስተዳደርን አስመልክቶ መቀሌ ላይ ያስተላለፈውን መልእክት እንደሚተገብረው ተስፋ እናደርጋለን፡፡ የመልካም አስተዳደር ችግር ትልቁ ችግር ነው፡፡ አብዛኛውን ጊዜያችንን ከስራ ይልቅ በቢሮክራሲ እያጠፋን ነው፡፡ መንግስት ይሄን መቅረፍ ከቻለ፣ እኛም ማደግ የምንችልበት ዓመት ይሆናል፡፡

Read 2505 times