Saturday, 03 October 2015 09:47

የለዛ ፕሮግራም ሽልማት ተካሄደ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

ከትናንት በስቲያ በተካሄደው የሸገር ኤፍ ኤም
102.1 የለዛ ፕሮግራም የአድማጮች ምርጫ  የኪነጥበብ ሽልማት በፊልምና በሙዚቃ ዘርፍ
የአመቱ የአድማጭ ምርጦች ተሸልመዋል፡፡

• በአመቱ ምርጥ ነጠላ ዜማ አሸናፊ የቴዲ አፍሮ (ቴዎድሮስ ካሣሁን) “ሠባ ደረጃ”
• በአመቱ ምርጥ የፊልም ማጀቢያ ዘርፍ ፀደንያ ገ/ ማርቆስ በ “ሃርየት” ፊልምማጀቢያ ሙዚቃ
• በአመቱ ምርጥ አዲስ ድምፃዊ ዘርፍ  ዳን አድማሱ
• በአመቱ ምርጥ አልበም
“አስታራቂ” የአብነት አጐናፍር
• በአመቱ ምርጥ የሙዚቃ ክሊፕ ድምፃዊ ዮሴፍ ገብሬ
• በአመቱ ምርጥ ፊልም ሰኔ 30
• በአመቱ ምርጥ ሴት ተዋናይት አዚዛ አህመድ በሰኔ 30 ፊልም
• በአመቱ ምርጥ የወንድ ተዋናይ ግሩም ኤርሚያስ በላምባ ፊልም
• በአመቱ የህይወት ዘመን ተሸላሚ ድምፃዊ አለማየሁ እሸቴ በመሆን ተሸልመዋል
የለዛ ፕሮግራም ሽልማት ተካሄደ ከትናንት በስቲያ በተካሄደው የሸገር ኤፍ ኤም
102.1 የለዛ ፕሮግራም የአድማጮች ምርጫ የኪነጥበብ ሽልማት በፊልምና በሙዚቃ ዘርፍ
የአመቱ የአድማጭ ምርጦች ተሸልመዋል፡፡
በአመቱ ምርጥ አልበም ዘርፍ የማዲንጐ አፈወርቅ “ስወድላት” እና የአብነት አጐናፍር “አስታራቂ”
አልበም ከፍተኛ ፉክክር የታየባቸው ሲሆን አስታራቂ 0.9 በመቶ ልዩነት ብቻ አሸናፊ ሆኗል፡፡

Read 3156 times