Saturday, 03 October 2015 09:48

የአቶ አቢሴሎም ይህደጐ የቀብር ስነስርአት ዛሬ ይፈፀማል

Written by  አለማየሁ አንበሴ
Rate this item
(4 votes)

   የአትሌቲክስ ስፖርት ወዳጅ የነበሩት የቀስተ ደመና ስፖንጅ ፋብሪካ ባለቤት አቶ አቢሴሎም ይህደጐ፤ ከትላንት በስቲያ ከዚህ አለም በሞት የተለዩ ሲሆን የቀብር ስነስርአታቸው ዛሬ ከቀኑ 9 ሰአት በጴጥሮስ ወጳውሎስ ቤተክርስቲያን ይፈፀማል፡፡ ባደረባቸው ህመም ለአንድ አመት ያህል በውጭ ሀገርና በሃገር ውስጥ ህክምና ሲከታተሉ የቆዩት አቶ አቤሲሎም፤ በ72 አመታቸው ነው ያረፉት፡፡
ከወላጅ አባታቸው ብላታ ይህደጐ ለማ እና ከእናታቸው ወ/ሮ ምትክ ተስፋዬ፣ ኤርትራ አስመራ ውስጥ የተወለዱት ባለሃብቱ፤ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርታቸውንም የተከታተሉት በአስመራ ነው፡፡ በአዲስ አበባ በስዊድሽ ሚሽንና በተፈሪ መኮንን ት/ቤት የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን መከታተላቸውንም ለማወቅ ተችሏል፡፡
ታዋቂው ባለሃብት አቶ አቤሴሎም የቀድሞ ሳምሶን ዳቦ ቤት ባለቤት እንደነበሩና በኋላም ቀስተደመና ስፖንጅ ፋብሪካን በማቋቋም ለበርካታ ወገኖች የስራ እድል እንደፈጠሩ  ከቤተሰቦቻቸው ያገኘነው መረጃ ይጠቁማል፡፡
አቶ አቤሴሎም የ3 ልጆች አባት ነበሩ፡፡

Read 4383 times