Saturday, 10 October 2015 16:37

ዙክበርግ ለስደተኛ ጣቢያዎች የኢንተርኔት አቅርቦት ሊያሟላ ነው

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

 የፌስቡኩ መስራች ማርክ ዙክበርግ በተለያዩ የአለማችን አገራት ለሚገኙ የስደተኞች መጠለያ ጣቢያዎች፣የኢንተርኔት አቅርቦት ለማሟላት እየተንቀሳቀሰ መሆኑን እንዳስታወቀ አሶሼትድ ፕሬስ ዘገበ፡፡ዙክበርግ ባለፈው ቅዳሜ በተከናወነው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ጠቅላላ ጉባኤ ላይ ተገኝቶ ባደረገው ንግግር፣ በስደተኞች መጠለያ ጣቢያዎች ውስጥ የሚገኙ ዜጎችን ከተቀረው አለም ጋር በመረጃ ለማስተሳሰር፣ የኢንተርኔት አቅርቦት የማሟላት እቅድ እንዳለው አስታውቋል፡፡
የኢንተርኔት አቅርቦት መሟላቱ ስደተኞች ከእርዳታ ድርጅቶችና ከለጋሾች የተሻለ ድጋፍ እንዲያገኙ የራሱን እገዛ ያደርጋል ያለው ዙክበርግ፣ በርቀት ከሚገኙ ቤተሰቦቻቸው ጋር እንዲገናኙም ያስችላቸዋል ብሏል፡፡
 ዙክበርግ በአለማ አቀፍ ደረጃ የኢንተርኔት ትስስር ለመፍጠርና ከ5 ቢሊዮን በላይ የተለያዩ አገራት ዜጎችን ተጠቃሚ ለማድረግ የሚያስችል ኢንተርኔት ዶት ኦርግ የተሰኘ ፕሮጀክት ከሌሎች አጋር ድርጅቶች ጋር በመተባበር እ.ኤ.አ ከ2013 ጀምሮ መተግበር እንደጀመረም ዘገባው አስታውሷል፡፡

Read 1384 times