ታዋቂው የኮምፒውተርና የስማርት ፎን አምራች ኩባንያ አፕል በዊስኮንሲን ማዲሰን ዩኒቨርሲቲ ስም የተመዘገበን የፈጠራ ውጤት በሚያመርታቸው አይፎን 5 ኤስ፣ አይፎን 6 እና አይፎን 6 ፕላስ ሞባይሎቹ ውስጥ ተጠቅሞ በመገኘቱ እስከ 862 ሚሊዮን ዶላር የሚደርስ ቅጣት ሊጣልበት እንደሚችል ተዘገበ፡፡ፕል ይህንን በዩኒቨርሲቲው ባለቤትነት ስር የሚገኝ የተለየ አይነት ፕሮሰሰር ከሞባይሎቹ በተጨማሪ በአንዳንድ የአይፖድ ምርቶቹ ውጥስ መጠቀሙን የጠቆመው የኢንዲፔንደንት ዘገባ፣ ኩባንያው ግን የዩኒቨርሲቲው የባለቤትነት መብት ውድቅ የተደረገ በመሆኑ ልወነጀል አይገባም ሲል ተከራክሯል፡፡
ጉዳዩን ሲመለከት የቆየው የማዲስን ፍርድ ቤት ግን ቴክኖሎጂውን የተጠቀምከው ባለቤቱን ሳታስፈቅድ ነው ሲል አፕልን ጥፋተኛ እንዳደረገውና ዊሊያም ኮንሊ የተባሉ ዳኛም አፕል በካሳ መልክ እስከ 862 ሚሊዮን ዶላር እንዲከፍል ሊፈረድበት እንደሚችል መናገራቸውን ዘገባው ገልጧል፡፡
Published in
ከአለም ዙሪያ