Saturday, 31 October 2015 08:41

አፕል በታሪኩ ከፍተኛውን የ53.4 ቢ. ዶላር ትርፍ አገኘ

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

   ታዋቂው የኮምፒውተርና ስማርት ፎን አምራች ኩባንያ አፕል፣ ባለፉት 12 ወራት የሸጣቸው አይፎን ስልኮች ቁጥር ክብረ ወሰን ማስመዝገቡንና ይህን ተከትሎም በታሪኩ ከፍተኛ የሆነውን የ53.4 ቢሊዮን ዶላር ትርፍ እንዳገኘ ማስታወቁን ዘ ቴሌግራፍ ዘገበ፡፡አፕል ባለፉት 12 ወራት ያገኘው አጠቃላይ ገቢ 233.7 ቢሊዮን ዶላር መሆኑን የጠቆመው ዘገባው፤ ይህም ኩባንያው በሳምንት ከ1 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ ወይም በእያንዳንዷ ሰከንድ ከ1ሺህ 693 ዶላር በላይ ትርፍ ማግኘቱን ያሳያል ብሏል፡፡ኩባንያው እስካለፈው መስከረም ወር በነበሩት ሶስት ወራት ገቢው በ22 በመቶ በማደግ 51.5 ቢሊዮን ዶላር መድረሱን ያስታወቀው አፕል ኩባንያ፤ በያዝነው ሩብ አመት ከ75.5 እስከ 77.5 ቢሊዮን ዶላር ሽያጭ አስመዘግባለሁ ብሎ
እንደሚጠብቅም ገልጿል፡፡ባለፉት ሶስት ወራት 48 ሚሊዮን አይፎን ስልኮችን እንደሸጠ የጠቆመው ኩባንያው፣ በተጠቀሰው ጊዜም ሽያጩ የ22 በመቶ እድገት ማሳየቱን አስታውቋል፡፡

Read 1182 times