Saturday, 07 November 2015 10:07

አማዞን የታተሙ መጽሐፍትን መሸጥ ጀመረ

Written by 
Rate this item
(2 votes)

   ባለፉት 20 አመታት በድረገጽ አማካይነት የተለያዩ ዲጂታል መጽሃፍትን ለሽያጭ በማቅረብ የሚታወቀው አማዞን፤የታተሙ መጽሃፍትን የሚሸጥበትን የመጀመሪያውን መደብር በሲያትል መክፈቱን ቢቢሲ ዘገበ፡፡
አማዞን ቡክስ የተሰኘው ይህ የመጽሃፍት መሸጫ መደብር የኩባንያውን የድረገጽ ሽያጭ መረጃዎች መሰረት አድርጎ የተመረጡ 6 ሺህ መጽሃፍትን ለሽያጭ ማቅረቡን የጠቆመው ዘገባው፣ የመጽሃፍቶቹ የመሸጫ ዋጋም ከድረገጽ የሽያጭ ዋጋ ጋር ተመሳሳይ እንደሆነ አመልክቷል፡፡
በአዲሱ መደብራችን የምንሸጣቸው መጽሃፍት የድረገጽ ሽያጭ ደንበኞቻችንን ፍላጎት፣ የቀረቡልንን የግዢ ጥያቄዎች፣ የመጽሃፍቱን ተወዳጅነትና ሌሎች ተያያዥ ጉዳዮችን መሰረት አድርገን የመረጥናቸው ናቸው ብለዋል፤ የአማዞን ኩባንያ ምክትል ፕሬዚደንት ጄኔፈር ካስት፡፡
አማዞን አዲሱ የመጽሃፍት መደብር የሚያስመዘግበውን ሽያጭ ገምግሞ፣ በቀጣይም በመላው አለም በሚገኙ የተለያዩ አካባቢዎች የታተሙ መጽሃፍትን መሸጫ መደብሮችን የመክፈት ዕቅድ እንዳለውም ተነግሯል፡፡
lone wolf attacks

Read 3326 times