አሜሪካ በ3 ወር ውስጥ ከ26 ሺህ 500 በላይ ተጠቃሚዎቼን መረጃ ጠይቃኛለች
ታዋቂው የማህበራዊ ድረገጽ ፌስቡክ፣ የተጠቃሚዎቹን የግል መረጃዎች አሳልፎ እንዲሰጣቸው የሚጠይቁት መንግስታት ቁጥር እያደገ መሆኑን ማስታወቁን ሲኤንቢ ኒውስ ዘገበ፡፡
መሰል መረጃዎችን አሳልፎ እንዲሰጣቸው ከመንግስታት የሚቀርቡለት ጥያቄዎች ቁጥር በ2015 የመጀመሪያዎቹ ሶስት ወራት ካለፈው አመት ተመሳሳይ ጊዜ ጋር ሲነጻጸር በ18 በመቶ ማደጉን የገለጸው ፌስቡክ፣ ባለፉት የጥር፣ የካቲትና መጋቢት ወራት ብቻ ከተለያዩ የአለም አገራት መንግስታት 41 ሺህ 214 ጥያቄ እንደቀረበለት አስታውቋል፡፡
የተጠቃሚዎቹን የግል መረጃ እንዲሰጡት ከጠየቁት መንግስታት መካከል የአሜሪካ መንግስት ቀዳሚውን ስፍራ እንደሚይዝ የጠቆመው ፌስቡክ፣ የአሜሪካ መንግስት በሶስቱ ወራት ከ26ሺህ 500 በላይ የሚሆኑ የፌስቡክ ተጠቃሚዎችን መረጃ አሳልፌ እንድሰጠው 17 ሺህ 577 ጥያቄዎችን አቅርቦልኛል ሲል ገልጧል፡፡
በተጠቀሰው ጊዜ ውስጥ ህንድ 5 ሺህ 115፣ እንግሊዝ 3 ሺህ 384፣ ፈረንሳይ 2 ሺህ 520፣ ጀርመን 2 ሺህ 344 መሰል ጥያቄዎችን እንዳቀረቡለት ያስታወቀው ፌስቡክ፣ የምመራበት ፖሊሲ የተጠቃሚዎቼን የግል መረጃ አሳልፌ እንድሰጥ ስለማይፈቅድልኝ ጥያቄያቸውን አላስተናገድኩም ብሏል፡፡
Saturday, 21 November 2015 14:55
ፌስቡክ የተጠቃሚዎችህን መረጃ ስጠን የሚሉኝ መንግስታት በዝተዋል አለ
Written by Administrator
Published in
ከአለም ዙሪያ
Latest from Administrator
- የእስራኤል እና የኢራን ፍጥጫ
- Insights on Israel's Response: Interview with Mr. Tomer Bar-Lavi, Chargé d’Affaires at the Embassy of Israel to Ethiopia
- Barr, a vocal Trump critic, says he will ‘support the Republican ticket’ in November
- Iran president warns of ‘massive’ response if Israel launches ‘tiniest invasion’
- "አልሞቷል" ፊልም ዛሬ በዓለም ሲኒማ ይመረቃል