Saturday, 21 November 2015 14:56

የጣሊያኗ ከተማ፤ ብስክሌት የሚጠቀሙ ነዋሪዎቿን ልትሸልም ነው

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

   አንድ ኪ. ሜትር ያሽከረከረ፣ 25 ሳንቲም ይሸለማል
    ማሳሮሳ የተባለችው የጣሊያን ከተማ ወደ ስራ ገበታቸው ሲጓዙ ከመኪና ይልቅ ብስክሌት የሚጠቀሙ ነዋሪዎቿን በወር እስከ 50 ዩሮ የሚደርስ ሽልማት እንደምትሰጥ ማስታወቋን ቢቢሲ ዘገበ፡፡የከተማዋ አስተዳደር ምክር ቤት፤ ብስክሌት ለሚጠቀም ነዋሪ በአንድ ኪሎ ሜትር 25 ሳንቲም ሂሳብ እየተሰላ ሽልማት እንዲሰጠው መወሰኑን የጠቆመው ዘገባው፣ አንደመነሻም ለ50 ሰራተኞች የአንድ አመት ሽልማት ለመስጠት ማሰቡንና በቀጣይም ሽልማቱን ለማስፋፋት ማሰቡን ገልጧል፡፡
በሽልማት መልክ የሚሰጠው ገንዘብ፣ ከትራፊክ ክፍያ ትኬት ከሚሰበሰበው የከተማዋ ገቢ እንደሚገኝ የተገለጸ ሲሆን፣ የከተማዋ አስተዳደር ሽልማቱን ለመስጠት ያሰበው ብስክሌት መጠቀም የትራፊክ መጨናነቅን ያስቀራል፣ የጤና ጠቀሜታም አለው በሚል መነሻ እንደሆነም ታውቋል፡፡ ባለፈው አመት በፈረንሳይ ተመሳሳይ የማበረታቻ ሽልማት መሰጠት ተጀምሮ እንደነበር ያስታወሰው ዘገባው፣ ይህም የብስክሌት ተጠቃሚዎችን ቁጥር ከፍ አድርጎት እንደነበር አክሎ ገልጧል፡፡

Read 2446 times