Tuesday, 29 December 2015 07:49

የነዳጅ ዋጋ ከ11 አመታት ወዲህ ከፍተኛውን ቅናሽ አሳየ

Written by 
Rate this item
(2 votes)

በበርሜል ከ37 ዶላር በታች ደርሷል

የአለም የነዳጅ መሸጫ ዋጋ ካለፉት 11 አመታት ወዲህ እጅግ ከፍተኛው ሆኖ የተመዘገበውን የዋጋ ቅናሽ በማሳየት በበርሜል ከ37 ዶላር በታች መድረሱን የነዳጅ አምራችና ላኪ አገራት ድርጅት ኦፔክ አስታወቀ፡፡
ባለፈው አመት በበርሜል ከ110 ዶላር በላይ ይሸጥ የነበረው ነዳጅ፣ ከፍተኛ የዋጋ ቅናሽ ሊያስመዘግብ የቻለው ከፍተኛ አቅርቦት በመኖሩና የአገራት የኢኮኖሚ እድገት እየተዳከመ ከመምጣቱ ጋር በተያያዘ የነዳጅ ፍላጎት እየቀነሰ በመምጣቱ ነው ሲል ኦፔክ ማስታወቁን ቢቢሲ ዘግቧል፡፡
በነዳጅ ላይ የዋጋ ቅናሽ መፈጠሩ እንግሊዝን በመሳሰሉ አገራት ለተጠቃሚዎች በርካሽ ዋጋ ነዳጅ የማግኘት እድል መፍጠሩን የጠቆመው ዘገባው፣ ይሄም ሆኖ ግን ከፍተኛ ቅናሽ ያሳየው የነዳጅ ዋጋው በአዲሱ አመት ይጨምራል ተብሎ እንደሚጠበቅ ኦፔክ መግለጹን አስረድቷል፡፡
የአለም የህዝብ ቁጥር እና የኢኮኖሚ እድገት የሃይል ፍላጎትን እስከ 2040 በግማሽ ያህል ያሳድገዋል ተብሎ እንደሚጠበቅ የገለጸው ኦፔክ፣ ከዚህ ጋር ተያይዞም የነዳጅ ፍላጎት ጭማሪ እንደሚያሳይ ግምቱን አስቀምጧል፡፡


Read 1496 times