Saturday, 02 January 2016 14:18

በአዲሱ ዓመት የአለም ኢኮኖሚ እድገት ይቀንሳል ተባለ

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

- ከ6 አመታት ወዲህ ዝቅተኛው ዕድገት እንደሚመዘገብ ይጠበቃል
በዋና ዋናዎቹ የአለማችን የበለጸጉ አገራት የተከሰተው የተቀዛቀዘ የኢኮኖሚ እድገትና ሌሎች አለማቀፍ ኔታዎች በሚያስከትሉት አሉታዊ ተጽዕኖ ሳቢያ በ2016 የአለም ኢኮኖሚ እድገት በእጅጉ ይቀንሳል ተብሎ
እንደሚጠበቅ አለማቀፉ የገንዘብ ተቋም ማስታወቁን ዘ ጋርዲያን ዘገበ፡፡
የተቋሙ ዳይሬክተር ክርስቲያን ላጋርድ ባለፈው ረቡዕ በሰጡት መግለጫ እንዳሉት፣ የ2006
የአለማችን የኢኮኖሚ እድገት እ.ኤ.አ በ2009 ከተከሰተው የኢኮኖሚ ቀውስ ወዲህ ዝቅተኛው ደረጃ ላይ ይደርሳል  ተብሎ ይጠበቃል፡፡ የኢኮኖሚ እድገቱ በ2014 አመት ከተመዘገበው 3.4 በመቶ እድገት በታች ይሆናል ያሉት  ዳይሬክተሯ፤ በ2015 በአለማቀፍ ንግድ እድገት ላይ ከፍተኛ ቅናሽ መታየቱን ጠቁመው በሸቀጦች ዋጋ ላይ የታየው  ቅናሽም ሃብትን መሰረት ያደረገ ኢኮኖሚ ባላቸው አገራት ላይ ተጽዕኖ ይኖረዋል ብለዋል፡፡በአዲሱ የፈረንጆች ዓመት ሩስያና ብራዚልን የመሳሰሉ አገራት የከፋ የኢኮኖሚ ችግር
እንደሚገጥማቸውም ዳይሬክተሯ ተናግረዋል፡፡ የምርታማነት መቀነስ፣ የአምራች ዜጎች ቁጥር ማሽቆልቆል፣ ከፍተኛ ብድር፣ አነስተኛ  ኢንቨስትመንትና የመሳሰሉት ጉዳዮች በአውሮፓና በሌሎች አገራት ኢኮኖሚ ላይ ተጽዕኖ እንደሚፈጥሩ ይጠበቃል ተብሏል፡፡

Read 2015 times