Saturday, 06 February 2016 10:27

የሴት ልጅ ግርዛት...ዛሬም አለ?

Written by 
Rate this item
(3 votes)

  አንድ በእድሜያቸው በግምት ወደ 60/ አመት የሆናቸው አባት ከሀያ አመት በፊት የሚከተለውን ምስክርነት

ሰጥተዋል፡፡
“...እኔ የኢትዮጵያ ሱማሌ ስሆን የምኖረው በጅግጅጋ ነው፡፡ ሴትን ልጅ መግረዝ በሕይወትዋ ላይ እንደመፍረድ

ይቆጠራል የሚል አቋም አለኝ፡፡ ከባለቤ የወለድኩዋቸው ሰባት ልጆች ሲሆኑ አራት ሴትና ሶስት ወንዶች ናቸው።

ለሶስቱ ሴቶች ባለመድረሴ መቸውንም የሚቆጨኝ ነገር ነው፡፡ ሳላስጥላቸው ልክ እንደእናታቸው ተገርዘዋል።

አንዱዋን ልጅ ግን አስጥዬ ወደዘመዶቼ አዲስ አበባ ስለላክሁዋት እሱዋ     አልተገረዘችም፡፡ ድናልኛለች፡፡
“በሴቶች ላይ የሚፈጸም ግርዛት ጀንደር ወይንም ስርአተ ጾታን መሰረት ያደረገ በሴቶች ላይ የሚፈጸም በደል ነው፡፡

ይህ ድርጊት የሴቶችን ሰብአዊ መብት የሚጋፋ መሆኑንም አለም የተስማማበት ጉዳይ ነው። ይህንንም መረጃ

በአለምአቀፍ ደረጃ ያሰራጨው የአለም የጤና ድርጅት ሲሆን አገራትም ያመኑበትና የተስማሙበት በመሆኑ ድርጊቱ

እንዲቆም ሲነገር አመታትን አስቆጥሮአል፡፡
በሴት ልጅ ላይ የሚፈጸም ግርዛት ሲባል በአይነት የተለያየ ሲሆን በብልት አካባቢ የስሜት ሰጪውን ክፍል ሳይነካ

ከሚፈጸመው ጀምሮ ጭርሱንም ሴቷን ስሜት የለሽ እስከሚያደርገው የግርዘት አይነት ድረስ በሶስት ደረጃ የተከፈለ

ነው፡፡ እንደ የአለም የጤና ድርጅት ዘገባ በግምት ከ100 እስከ 140 ሚሊዮን ልጃገረዶችና ሴቶች በአለምአቀፍ ደረጃ

ግርዛት የተፈጸመባቸው ሲሆን ወደ 3/ ሚሊዮን የሚጠጉ ልጃገረዶች  በየአመት በተለይም በአፍሪካ ድርጊቱ ግርዘቱ

ይፈጸምባቸዋል፡፡
በአፍሪካ የሚተገበረውን የሴት ልጅ ግርዛት ለመገመት እንደተቻለው ወደ 98/ በመቶ የሚሆነው በሶማሊያ የሚፈጸም

ሲሆን በንጽጽሩ ደግሞ በኡጋዳ 1/ በመቶ ብቻ ይፈጸማል፡፡የቅርብ ጊዜ ጥናት እንደሚያሳየው ወደ 91.5 ሚሊዮን

የሚሆኑ እድሜያቸው ከ9/ አመት በላይ የሆኑ በአፍሪካ ያሉ ልጃገረዶች  በግርዛት ምክንያት ከሚደርሱ የተለያዩ

ችግሮች ጋር የሚኖሩ መሆኑ ተረጋግጦአል። በኢትዮያ በተካሄደውሃመ ዲሞግራፒክ ኤንድ ኼልዝ ሰርቬይ ወደ 74/

በመቶ የሚሆኑ ልጃገረዶችና ሴቶች በተለያዩ መስተዳድሮች ከሶስቱ አንዱ አይነት ግርዘት እንደተካሄደባቸው ያሳያል፡፡

የሴት ልጅ ግርዛት በቅርብእና በርቀት ወይንም በወደፊት የጤና ሁኔታ ላይ የተለያዩ ችግሮችን እንደሚያስከትል ግልጽ

ነው፡፡ እንደየአለም ጤና ድርጅት መረጃ ግርዘት የተከናወነባቸው ሴቶች በተለይም ልጅ በመውለድ ጊዜ ለተለያዩ

ችግሮች እንደሚጋለጡ ነው፡፡ ይህ ችግርም እንደግርዘቱም አይነት ደረጃው እንደሚለያይ ተጠቁሞአል፡፡
በቅርብ ጊዜ ማለትም በ2013/ በኖርዌይ በተደረገ ጥናት መመልከት እንደሚቻለው ሴቶች በተለይም በሶስተኛ ደረጃ

ያለውን እና በከፋ ሁኔታ የሚፈጸመውን ግርዘት በመገረዛቸው ምክንያት በወሊድ ጊዜ የማህጸን መተርተር፣ በመሳሪያ

ድጋፍ መውለድ በመጎተት፣ የማህጸን መድማት እና አስከፊ በሆነ ሁኔታ ልጅን መገላገል ሊያጋጥማቸው እንደሚችል

ተገልጾአል፡፡
በኢትዮጵያ በሶስተኛ ደረጃ የሚተገበረው እና በሶማሊያ ክልል የሚፈጸመው የግርዛት አይነት እናቶች በወሊድ ጊዜ

በከፍተኛ ሁኔታ እንዲሰቃዩ እና በተራዘመ ምጥ ምክንያትም ልጆቻቸውን እንዲያጡ ምክንያት ሊሆን እንደሚችል

ግልጽ ነው፡፡
በኢትዮጵያ ዛሬም በሶማሊያ ክልል በሶስተኛው አይነት ግርዛት ምክንያት ብዙ ሴቶች የሚሰቃዩ ሲሆን ዲሴምበር

2015/ ይፋ በሆነው ጥናትም እንደተጠቆመው ወደ 97/ በመቶ የሚሆኑ ሴቶች የችግሩ ሰለባ ሆነዋል። በእርግጥ

በኢትዮጵያ በሶማሊያ ክልል ችግሩ በስፋት መኖሩ ቢታወቅም ከዚህ ጋር ተያይዞ በመውለድ ጊዜ ያጋጠሙ ችግሮች

በግልጽ ተመዝግበው የተቀመጡበት አሰራር ባለመኖሩ ሁኔታውን ለመረዳት አስቸጋሪ መሆኑን ጥናቱ ጠቁሞአል፡፡

በዚህም መሰረት በሶማሌ ክልል ጅግጅጋ በተለይም በካራማራ ሆስፒታል እንደውጭው አቆጣጠር ከጃንዋሪ 2015/

እስከ ማርች 2015/ ድረስ የተደረገ ጥናት ወደሆስፒታሉ  ለመውለድ የሚመጡ ሴቶችን ከግርዛት ጋር በተያያዘ በምጥና

ወሊድ ወቅት ምን ችግር አንደሚከሰትባቸው ለይቶ ለማወቅ እንዲረዳ በዶ/ር ሙታሲም አብዱላሂ እና ዶ/ር ወንድሙ

ጉዱ ጥናት ተደርጎአል፡፡
ኦርጋናይዜሽን ፎር ዘ ድቭሎፐምነንት ፎር ውመን ኤንደ ችልድረን ኢትዮጵያ በሚባል በጎ አድራጊ ድርጅት

አስተባባሪነት እና ሌሎች የሚመለከታቸው እና ድጋፍ ሰጪ አካላት ትብብር የተሰራው ጥናት ይፋ በተደረገበት ወቅት

ጥናት አድራጊዎቹ ስለጥናቱ ለአምዱ አዘጋጅ ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡
ለመሆኑ ዛሬም ግርዛት አለ? ተብለው ለተጠየቁት ዶ/ር ሙታሲም የሚከተለውን መልስ ነበር የሰጡት፡፡
“...ግርዛት በኢትዮያ ውስጥ ዛሬም አለ፡፡ ግርዛት መኖሩን በመገናኛ ብዙሀንም በተለያየ ጊዜ ሲነገር የሚሰማ ሲሆን ሃመ

በተደረገው ጥናትም  74/ በመቶ የሚሆኑ ሴቶች የተገረዙ መሆኑ ተረጋግጦአል፡፡ የግርዛት አይነቱ በሶስት ደረጃ

የተከፈለ ሲሆን 3ተኛ የሚባለው ግርዛት እጅግ አስከፊና ሴቶችን የሚጎዳ ነው፡፡ ይህ አይነቱ ግርዘት በአገር አቀፍ ደረጃ

ትንሽ ፐርሰንት ሲሆን በሶማሌ ክልል ግን ከ80/ በመቶ በላይ ሶስተኛውን አይነት ግርዛት የተገረዙ ሴቶች አሉ፡፡

በእርግጥ እኛ ያጠናነው ጥናት ዛሬ የተገረዙትን የሚመለከት ሳይሆን የዛሬ ሀያ እና ከዚያም በላይ በሆኑ አመታት

የተገረዙትንና በወሊድ ወቅት ምን ችግር እንደሚያጋጥማቸው በካራማራ ሆስፒታል ተገኝተን የተመለከትንበት ነው፡፡

በምጥ ሰአት እንደሚቸገሩ እና ልጁ በተገቢው ጊዜ የመውጣት ችግር ፣ካር ለማስገባት ችግር እንደሚያጋጥም፣

የመድማት ሁኔታ እና የመሳሰሉት እንደሚኖሩ በጥናቱ አረጋግጠናል።”
ሌላው ጥናት ያካሄዱት ዶ/ር ወንድሙ ጉዱ ናቸው። እሳቸውም አንደሚሉት፡-
“...ግርዛት በተለያዩ ጥናቶች እንደቀረበው 90/በመቶ እና ከዚያ በላይ የሚፈጸም ሲሆን አስከፊውን አይነት ግርዛት

የተገረዙት ሴቶች ደግሞ ከ84-85 በመቶ የሚሆኑት ናቸው፡፡” ብለዋል፡፡
ጥናቱ በተካሄደበት ወቅት ግርዛት የተፈጸመባቸውንና ያልተገረዙ ሴቶችን ሁኔታም ለማነጻጸር ተሞክሮአል። በወሊድ

ጊዜ የሚያጋጥሙ ችግሮች በሙሉ ማለት ይቻላል... በተደጋጋሚ የሚያጋጥሙት በተገረዙ ሴቶች ላይ መሆኑ ሲረጋገጥ

ያልተገረዙት ላይ ግን እጅግ በተራራቀ እና አልፎ አልፎ በሚባል ሁኔታ የሚታይ ነው።
ዶ/ር ሙታሲም  እንደገለጹትም ...
“...በሱማሌ ክልል ያሉ ሴቶች ግርዛቱ ትክክል እንዳልሆነ እና በተለይም በወሊድ ወቅት አደጋ እንደሚያስትል

ያምናሉ፡፡ ነገር ግን ድርጊቱን ለማስቀረት በቀላሉ የማይቻል በመሆኑ አሁንም አይደረግም ለማለት አይቻልም፡፡

ግርዛቱን ከሚፈጽሙት ግለሰቦች ጀምሮ አስፈጻሚዎቹ ቤተሰቦች በባህል በኢኮኖሚና በማህበራዊ ትስስር ምክንያት

በቀላሉ ሊያስቀሩት እንዳልቻሉ ለማየት ተችሎአል፡፡”
ጥናቱ በተካሄደበት ወቅት ግርዛት የተፈጸመባቸውንና ያልተገረዙ ሴቶችን ሁኔታም ለማነጻጸር ተሞክሮአል። በወሊድ

ጊዜ የሚያጋጥሙ ችግሮች በሙሉ ማለት ይቻላል... በተደጋጋሚ የሚያጋጥሙት በተገረዙ ሴቶች ላይ መሆኑ ሲረጋገጥ

ያልተገረዙት ላይ ግን እጅግ በተራራቀ እና አልፎ አልፎ በሚባል ሁኔታ የሚታይ ነው።
ዶ/ር ወንድሙ ከላይ የተሰጠውን አስተያየት በማጠናከር እንዴት ማስቀረት ይቻላል? ለሚለው፡-
“...በእርግጥ ግርዛቱ በኢትዮጵያ በተለያዩ መስተዳድሮች መፈጸሙ አልቀረም ቢባልም አይነቱ ግን በሶማሌ እና

ተመሳሳይ አካባቢዎች እንደሚፈጸመው 3ተኛው አይነት ማለትም አስከፊው አይደለም፡፡ ባጠቃላይ ግን የትኛውንም

አይነት በየትኛውም ቦታ በሴቶች ላይ ግርዛቱ እንዳ ይፈጸም ለማድረግ ሲፈለግ ብዙ ነገሮችን መነካካት ያስፈልጋል፡፡

ለምሳሌም፡-
ሴቶች እንዳይገረዙ የህግ ከለላ መስጠት፣ ፖሊሲ መንደፍ፣
የሴቶችን የወሳኝነት አቅም ማሳደግ፣
የሴት ልጅ ግርዛት እንዲኖር የሚያስችሉ ምክንያቶች ምን እንደሆኑ በጥናት አረጋግጦ አስፈላጊውን እርምጃ መውሰድ፣
ወንዶች በጉዳዩ እንዲሳተፉ ማድረግና የተገረዘች ላግባ አላግብ የሚለውን ሀሳብ ለመወሰን የሚያስችላቸውን አቅም

እንዲያጎለብቱ እና ግርዘትን እንዲያወግዙ ማድረግ፣
የሀይማኖት መሪዎች፣ የቀበሌ፣ የጎሳ አስተዳዳሪዎች የመሳሰሉ ኃላፊነት ቦታ የተቀመጡ ሰዎችም የጉዳዩን አስከፊነት

ተገንዝበው ድርጊቱን ለማስቆም እንዲተባበሩ ማድረግ ያስፈልጋል፡፡
ባጠቃላይም በተናጠል የሚሰራ ስራ ውጤታማ ስለማያደርግ በተቀናጀ መልኩ የሚመለከተው ሁሉ ተሳትፎ የየበኩሉን

እርምጃ በመውሰድ የሴት ልጅ ግርዛት እንዲቆም ማድረግ ይቻላል፡፡ “ ብለዋል ዶ/ር ወንደሙ ጉዱ፡፡
ከላይ ለመግለጽ እንደተሞከረው ግርዛት በሶስት ደረጃ ተከፍሎአል፡፡ በኢትዮጵያ ያለውን የግርዛት አይነት ስንመለከት

በሰሜኑ እና በአንዳንድ የሐገሪቱ ክፍል ሲፈጸም የኖረው  አንዱ ሲሆን ሁለተኛውና ሶስተኛው በተለያዩ አካባቢዎች

እንደሶማሌ አፋር ከምባታ አካባቢ ሲፈጸሙ የነበሩ ናቸው፡፡ ሲፈጸሙ /ምየሚለውን አባባል የተጠቀምነው እነዚህ

ድርጊቶች በአሁኑ ወቅት ምን ያህል አይተገበሩም ለሚለው ማረጋገጨ ለጊዜው እጃችን ላይ ስለሌለ ነው፡፡

Read 5149 times