Print this page
Saturday, 13 February 2016 11:06

የዘላለም ጥግ

Written by 
Rate this item
(12 votes)

(ስለ እግዚአብሔር)

- እግዚአብሔር ህመማችንን የምንለካበት
ፅንሰ ሀሳብ ነው፡፡
ጆን ሌኖን
- እግዚአብሔር ረቂቅ ነው፤ ተንኮለኛ ግን
አይደለም፡፡
አልበርት አንስታይን
- እግዚአብሔር ራሳቸውን የሚረዱ ሰዎችን
ይረዳል፡፡
ቤንጃሚን ፍራንክሊን
- ከእግዚአብሔር ጋር አወራለሁ፤ ሰማዩ ግን
ባዶ ነው፡፡
ሲልቪያ ፕላዝ
- በእግዚአብሔር አላምንም፤ ግን ይናፍቀኛል፡

ጁሊያን ባርነስ
- እያንዳንዱ ሰው በራሱ መንገድ ወደ
እግዚአብሔር ዘንድ ይምጣ፡፡
ሔነሪ ዋርድ ቢቼር
- ከሰው ልጅ መፍትሄዎች ይልቅ
የእግዚአብሔር እንቆቅልሾች የበለጠ
ያጠግባሉ፡፡
ጂ.ኬ. ቼስቴርቶን
- እግዚአብሔር ዛሬ የ86ሺ 400 ሰከንዶች
ስጦታ አበርክቶልሃል፡፡ ከእነዚህ ውስጥ
አንዱን ሰከንድ “ተመስጌን” ለማለት
ተጠቅመህበታል?
ዊሊያም አርተር ዋርድ
- እግዚአብሔር ወንጌልን በመፅሃፍ ቅዱስ
ላይ ብቻ አልፃፈም፤ በዛፎች፣ በአበቦች፣
በደመናውና በክዋክብቶችም ላይ ጭምር
እንጂ፡፡
ማርቲን ሉተር
- እግዚአብሔር ሁለት እጆችን ሰጥቶናል፡፡
አንደኛውን ልንቀበልበት፣ ሌላኛውን ደግሞ
ልንሰጥበት፡፡
ቢሊ ግራሃም
- እግዚአብሔር ዓለምን ለመፍጠር ውብ
የሂሳብ ስሌት ተጠቅሟል፡፡
ፖል ዲራክ
- እግዚአብሔር ሰዎች ከሚያስቡት በላይ
ትልቅ ነው፡፡
ጂሚ ዲን
- እግዚአብሔር ቁማር አይጫወትም፡፡
አልበርት አንስታይን
- እግዚአብሔር ትላልቆቹን ክብደቶች
የሚያንጠለጥለው በትናንሾቹ ሽቦዎች ላይ
ነው፡፡
ፍራንሲስ ቤከን

Read 4106 times
Administrator

Latest from Administrator