Saturday, 20 February 2016 10:05

1 ሚ. አፍሪካውያን ህጻናት ተረብዋል

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

   በምስራቅና ደቡባዊ አፍሪካ አገራት የሚገኙ 1 ሚሊዮን ያህል ህጻናት የኤሊኖ ክስተት ባስከተለው ድርቅ ሳቢያ የከፋ የምግብ እጥረት ተጠቂዎች መሆናቸውንና አስቸኳይ እርዳታ እንደሚያስፈልጋቸው ዩኒሴፍ አስታወቀ፡፡ በአካባቢው አገራት የሚገኙት እነዚህ ህጻናት የምግብና የውሃ እጥረት እንዳለባቸውና የክብደት መጠናቸው እየቀነሰ እንደሚገኝ የጠቆመው ተቋሙ፣ የምግብ ዋጋ መናር ቤተሰቦች ሳይመገቡ እንዲውሉና ንብረቶቻቸውን ሽጠው ምግብ እንዲገዙ እያስገደዳቸው ነው ብሏል፡፡መንግስታት ችግሩን ለመቋቋም የራሳቸውን ጥረት እያደረጉ ቢሆንም፣ በህጻናቱ ላይ የተከሰተው የከፋ የምግብ እጥረት አሳሳቢ ነው ተብሏል፡፡ሌሴቶ፣ ዚምባቡዌና አብዛኞቹ የደቡብ አፍሪካ አገራት ድርቁን ተከትሎ አስቸኳይ እርዳታ እንደሚፈልጉ ማስታወቃቸውን የዘገበው አጃንስ ፍራንስ ፕሬስ፣ በኢትዮጵያም የምግብ እርዳታ የሚያስፈልጋቸው ሰዎች ቁጥር በዚህ አመት ከ10 ሚሊዮን ወደ 18 ሚሊዮን ከፍ ይላል ተብሎ እንደሚጠበቅ ገልጧል፡፡ማላዊ ባለፉት 9 አመታት የከፋ በተባለው የምግብ እጥረት እንደተጠቃች ያስታወሰው ዘገባው፣ 15 በመቶ ያህል ህዝቧ የርሃብና የከፋ የምግብ እጥረት ችግር እንዳንዣበበበት አክሎ ገልጧል፡፡

Read 1847 times Last modified on Saturday, 20 February 2016 10:09