Saturday, 20 February 2016 10:06

ርካሹ የዓለማችን ስማርት ፎን ለገበያ ሊቀርብ ነው

Written by 
Rate this item
(5 votes)

    ሪንጊንግ ቤልስ የተባለው የህንድ የሞባይል ቀፎዎች አምራች ኩባንያ፣ በዓለማችን የስማርት ፎን ገበያ እጅግ ርካሽ ዋጋ የተተመነለትን ፍሪደም 251 የተባለ አዲስ የሞባይል ቀፎ ምርቱን በአንድ አመት ጊዜ ውስጥ ለገበያ እንደሚያቀርብ አጃንስ ፍራንስ ፕሬስ ዘገበ፡፡ከጥቂት ወራት በፊት የተቋቋመው ኩባንያው፣ለዚህ የሞባይል ቀፎ 7.3 ዶላር የመሸጫ ዋጋ የተመነለት ሲሆን የሞባይል ቀፎው 8 ጊጋ ባይት ሚሞሪ ያለውና በፊቱና በኋላው ሁለት ካሜራዎች የተገጠሙለት ነው ተብሏል፡፡ ኩባንያው በቅርቡም በአገሪቱ የ4ጂ የሞባይል ቀፎ ገበያ እጅግ እርካሹ ዋጋ የተተመነለትን ምርቱን ለገበያ ማብቃቱን ያስታወሰው ዘገባው፣ አዲሱን የሞባይል ቀፎውን የመገጣጠም ስራውን እንደጀመረና ምርቱን በአንድ አመት ጊዜ ውስጥ ለአገር ውስጥ ገበያ ያቀርባል ተብሎ እንደሚጠበቅም አስረድቷል፡፡
ህንድ በአለማችን የሞባይል ቀፎ ገበያ ሁለተኛ ደረጃ ላይ እንደምትገኝ የጠቆመው ዘገባው፣ በአገሪቱ አንድ ቢሊዮን ያህል የሞባይል ስልክ ተጠቃሚዎች እንዳሉም ገልጧል፡፡

Read 2845 times