Saturday, 19 March 2016 11:38

ኢትዮጵያ ለሱዳን የአሣ ቋንጣ እያቀረበች ነው

Written by 
Rate this item
(5 votes)

የሰሜን ጐንደር ዞን አሣ አስጋሪዎችና ነጋዴዎች ወደ ሱዳን የደረቀ የአሣ ቋንጣ እየላኩ ሲሆን በዘንድሮ አመት በ6 ወር ጊዜ ውስጥ ከ12 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ ማግኘታቸው ታውቋል፡፡
አሣ አስጋሪዎቹና ነጋዴዎቹ ከጣና ሃይቅ የሚያሰግሩት እርጥብ አሣ በአካባቢው ባለው የገበያ ችግር ውሎ ሲያድር ይበላሽባቸው እንደነበር ገልፀው ለሱዳን ገበያ አሣውን አድርቀው በቋንጣ መልክ ማቅረብ መጀመራቸው ከኪሣራ አላቆ ትርፍ በትርፍ እንዳደረጋቸው ገልፀዋል፡፡
በሰሜን ጐንደር ዞን በጣቁሣ ወረዳ ዶልጊ ከተማ የሚገኙት አስጋሪዎችና ነጋዴዎቹ ምርታቸው በሱዳን ገበያ በእጅጉ ተፈላጊ እየሆነ መምጣቱን ጠቁመዋል፡፡
ወደ 200 የሚሆኑት አስጋሪዎቹና ነጋዴዎቹ በግማሽ አመቱ 4 መቶ ሺህ ኪሎ ግራም የአሣ ቋንጣ አዘጋጅተው በመተማ በኩል ለሱዳን ማቅረባቸውም ከመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት የተገኘው መረጃ ጠቁሟል፡፡  

Read 2144 times