Saturday, 28 May 2016 15:46

ኬንያ የአለማችን ትልቁን የስደተኞች መጠለያ መዝጋቷን ተመድ ተቃወመ

Written by 
Rate this item
(2 votes)

ከ 300 ሺ በ ላይ ሶማሊያውያን ስ ደተኞችን ወደ አገራቸው ለመመለስ ወ ስናለች
          ኬንያ በአለማችን በትልቅነቱ ቀዳሚውን ስፍራ የሚይዘውን የዳዳብ የስደተኞች መጠለያ ጣቢያ ለመዝጋት መወሰኗን የአገሪቱ ምክትል ፕሬዚዳንት ዊሊያም ሩቶ መግለጻቸውን ተከትሎ፣ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ውሳኔውን እንደሚቃወመው ማስታወቁን ኦል አፍሪካን ዶት ኮም ዘገበ፡፡
የተመድ ዋና ጸሃፊ ባንኪ ሙን፤ ኬንያ ግዙፉን የስደተኞች መጠለያ ጣቢያ ለመዝጋት መወሰኗ፣ በመጠለያ ጣቢያው ውስጥ የሚገኙ በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ስደተኞችን ለከፋ አደጋና ጥፋት የሚዳርግ በመሆኑ ውሳኔውን እንደሚቃወሙት ማስታወቃቸውን ዘገባው ጠቁሟል፡፡ የኬንያ ምክትል ፕሬዚዳንት ዊሊያም ሩቶ ባለፈው ሰኞ በቱርክ መዲና ኢስታምቡል በተካሄደው የዓለማችን የሰብዓዊ ጉዳዮች ጉባኤ ላይ የአገሪቱ መንግስት የስደተኞች መጠለያ ጣቢያውን በመዝጋት 300 ሺህ ያህል ሶማሊያውያን ስደተኞችን ወደመጡበት ለመመለስ ያሳለፈው ውሳኔ የማይቀለበስ ነው ሲሉ መናገራቸውን ያስታወሰው ዘገባው፣ አለማቀፉ ማህበረሰብ ስደተኞቹን መልሶ ለማስፈር ተገቢውን ድጋፍ እንዲያደርግ ጥሪ ማቅረባቸውንም አመልክቷል፡፡ የኬንያ መንግስት የስደተኞች መጠለያ ጣቢያዎችን በአንድ አመት ጊዜ ውስጥ ሙሉ ለሙሉ ለመዝጋት የወሰነው፣ የሽብርተኞች መደበቂያና ለአገሪቱ ደህንነት ስጋት በመሆናቸውና ለአካባቢው አደጋ ስለሆኑ ነው ማለቱን የጠቆመው ዘገባው፣ተመድ ውሳኔውን ተቃውሞታል፡፡

Read 2240 times