Saturday, 11 June 2016 13:38

መንግስት በአሜሪካ ቦንድ ሽጦ ያገኘውን 6.5 ቢ. ዶላር ሊመልስ ነው

Written by 
Rate this item
(7 votes)

ለ3 ሺህ 100 ዲያስፖራዎች የሸጠው ቦንድ ህገ-ወጥ ነው ተብሏል
መንግስት ጥፋቱን አምኖ ገንዘቡን ለመክፈል ተስማምቷል

የኢትዮጵያ መንግስት ለታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ገቢ ለማሰባሰብ በማቀድ በአሜሪካ ለሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ያደረገው የቦንድ ሽያጭ የአሜሪካ ህግ ከሚፈቅደው ውጪ በመሆኑና ህገወጥ መሆኑ በመረጋገጡ፣ ከሽያጩ ያሰባሰበውን 5.8 ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር ጨምሮ በድምሩ 6.5 ቢሊዮን ዶላር መልሶ እንዲከፍል ተወሰነበት፡፡
የአሜሪካ የቦንድ ሽያጭና ግዢ የሚቆጣጠረው ሴኪዩሪቲስ ኤንድ ኤክስቼንጅ ኮሚሽን የተባለ ተቋም ከትናንት በስቲያ እንዳስታወቀው፣ የኢትዮጵያ መንግስት እ.ኤ.አ ከ2011 እስከ 2014 ባሉት አመታት የአሜሪካ ህግ ከሚፈቅደው ውጪ፣ በአገሪቱ ለሚኖሩ ከ3 ሺህ 100 በላይ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ባከናወነው ያልተመዘገበ የቦንድ ሽያጭ፣ የሰበሰበውን 5.8 ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር እና 601 ሺህ የአሜሪካ ዶላር የወለድ ገንዘብ መልሶ እንዲከፍል ውሳኔ ተላልፎበታል፡፡
ተገቢውን ምዝገባ ሳያሟላ በአሜሪካ ዋና ዋና ከተሞች የባለሃብቶች ስብሰባዎችን በማካሄድ፣ የቦንድ ሽያጭ ማስታወቂያዎችን በኢምባሲው ድረ ገጽ፣ በሬዲዮና በቴሌቪዥን በማስተላለፍና ሽያጩን በማከናወን ህገወጥ ተግባር ፈጽሟል የተባለው የኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ሃይል አገልግሎት በበኩሉ የፈጠመውን ጥፋት በማመን፣ የተጠቀሰውን ገንዘብ እንዲመልስ የተላለፈበትን ውሳኔ ተቀብሎ ለመክፈል መስማማቱንም ኮሚሽኑ ባወጣው መግለጫ አስታውቋል፡፡ ከኢትዮጵያ መንግስት ቦንድ የገዙ የዲያስፖራ ባለሃብቶች ያወጡትን ገንዘብ ከነወለዱና ከነካሳው እንደሚያገኙም ኮሚሽኑ አስታውቋል፡፡

Read 1650 times