Saturday, 18 June 2016 13:27

አገር አቀፍ ተጓዥ የንግድ ባዛር ለ1 ዓመት ይቀጥላል

Written by 
Rate this item
(2 votes)

የኢትዮጵያ አካል ጉዳተኞች ብሔራዊ ማህበርና መስከረም ፕሮሞሽን በመተባበር ያዘጋጁት “አገር አቀፍ ተጓዥ የንግድ ትርኢትና ባዛር” ባለፈው ሳምንት መጨረሻ ተከፈተ፡፡ “አካል ጉዳተኞችን ማሳተፍ የህዳሴው አካል ነው” በሚል መርህ የመጀመሪያውን የንግድ ትርኢትና ባዛር ሜክሲኮ አደባባይ የከፈተው ማህበሩ፤ በተለያዩ የክልል ከተሞች ለ1 ዓመት እንደሚቀጥል አስታውቋል፡፡
ከተቋቋመ 23 ዓመታትን ያስቆጠረውና በአገር አቀፍ ደረጃ 16ሺህ አባላት ያሉት ማህበሩ፤ የአካል ጉዳተኞችን መብት ለማስከበርና በሁሉም ዘርፍ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ለማስቻል ጥረት ሲያደርግ መቆየቱን አስታውሶ፤ አካል ጉዳተኞች አካል ጉዳተኝነታቸው ሳይገድባቸው የሚያመርቷቸውን ምርቶች ከገዢ ጋር ለማገናኘትና ለማበረታታት ባዛሩ መዘጋጀቱን የማህበሩ ሃላፊዎች ባለፈው ረቡዕ በመክፈቻ ስነ-ስርዓቱ ላይ ተናግረዋል፡፡
በንግድ ትርኢትና ባዛሩ ላይ አካል ጉዳተኖች ያመረቷቸው ቆዳና የቆዳ ውጤቶች፣ የእጅ ስራዎች፣ ቦርሳዎች፣ ቀበቶዎች፣ የሶፋ ጨርቆች፣ የህትመትና የማስታወቂያ ስራዎችና ሌሎችም እቃዎች ለእይታና ለሽያጭ እንደሚቀርቡ ተገልጿል፡፡

Read 1227 times