Saturday, 25 June 2016 12:19

ፌስቡክ በአሜሪካ እና ፌስቡክ በኢትዮጵያ

Written by 
Rate this item
(25 votes)

• የበሽታው ተጠቂ በ24 ሰዓት ህክምና ካላገኘ ለሞት ሊዳረግ ይችላል



ፌስቡክ በአሜሪካ
አንዲት አሜሪካዊት እንዲህ ብላ ፖስት አደረገች፡- “ሀይ ጋይስ! rly ዛሬ በጣም ጨንቆኛል፡፡
ከሳምንት በፊት አንዲት ጓደኛዬ ፍቅረኛዋን አስተዋውቃኝ ነበር፡፡ ግን ድንገት ሳላውቅ ከልጁ ጋር
ፍቅር ያዘኝ፡፡ እንዳልነግረው ደሞ የጓደኛዬ ፍቅረኛ ስለሆነ ፈራሁ፡፡ በጣም ጨንቆኛል፤ ሀሳባችሁን
አካፍሉኝ”
አሜሪካውያን ኮሜንት መስጠት ይጀምራሉ፡-
Johnson= አይዞሽ ቆንጆ፤እንደዚህ አይነት ነገር ያጋጥማል፤more ደሞ ከቤተሰቦችሽ ጋር
ብትንጋገሪበት ጥሩ ይመስለኛል፡፡
Anita Brown= oh! እኔም እንደዚህ አይነት ነገር አጋጥሞኝ ያውቃል፡፡ ነገር ግን ከልጁ ጋር
በመነጋገር ችግሩን ለመፍታት ችያለሁ፡፡ አንቺም ለልጁ ብትነግሪው ሊቀልሽ ይችላል፡፡
Michael= በውይይት የማይፈታ ነገር የለም፡፡ so ሶስታችሁም ቁጭ ብላችሁ ብትወያዪ ጥሩ
ይመስለኛል፡፡ ጭንቀት ግን ለጤናሽ ጥሩ አይደለም፡፡
Devid Jackson= ብዙም አትጨነቂ፤ይሄ እኮ ምንም ማለት አይደለም፡፡ ለሰው መናገር ከፈራሽ
ደሞ የተለያዪ የሳይኮሎጂ መፅሀፎችን በማንበብ እራስሽን ለማረጋጋት ሞክሪ፡፡

ፌስቡክ በኢትዮጰያ

አንዲት ኢትዮጵያዊት ደግሞ በተመሳሳይ የሚከተለውን ፖስት አደረገች፡-
“ሀይ፤ ስሜ ቅድስት ይባላል፡፡ የምኖረው እዚሁ አዲስ አበባ ነው፡፡ ባልጠበኩት መንገድ ከጓደኛዬ
ፍቅረኛ ጋር ፍቅር ያዘኝ፡፡ ምን ማድረግ እንዳለብኝ ግራ ገብቶኛል፡፡
በናታችሁ ሀሳባችሁን አካፍሉኝ፡፡”
ኢትዮጵያውያን ኮሜንት መስጠት ጀመሩ፡-
Alemayew Kasahun= ወይ ስምንተኛው ሺ! ደሞ አፍ አለኝ ብለሽ ታወሪያለሽ እንዴ? ወራዳ!
Selam Habeshawit= ኧረ ስንት አይነት ሰው አለ ግን በጌታ! በናትሽ እንደዚህ አይነት ወሬ
እያወራሽ እኛ ሴቶችን አታሰድቢ፡፡
Biniyam Ye Ortodox Lij= እግዚኦ ማህርና ክርስቶስ!! ምን አይነት ዘመን ላይ ነው ግን ያለነው፡፡
እሱ ይቅር ይበልሽ፡፡
Yonas Fikru= እውነት ግን አንቺ ኢትዮጵያዊት ነሽ?
Teddy Man= ታዲያ እኛ ምናገባን? የቤትሽን አመል እዛው! እኛ እንደዚህ አይነት ነገር
አይመቸንም፡፡
Jemal Seid= ያ አላህ!! እንደዚህ በቁሜ ከምዋረድ ብሞት ይሻለኛል፡፡
Betelhem kiros= ደሞ ስምሽን ማነው ቅድስት ብሎ ያወጣልሽ?? እርጉም ቢሉሽ ይሻል ነበር፡፡
በእውነት አፈርኩብሽ፡፡ አምላኬ ሆይ የሚያደርጉትን አያውቁምና ይቅር በላቸው፡፡
Daniel Love= ወይ ሴቶች በቃ መጨረሻችሁ እንደዚህ ሆነ ማለት ነው? ሴት በዛ ጎመን ጠነዛ አሉ!
ምንጭ፦ Kalid Alfarsi Ahmed
(ከማፉዝ መሃመድ ፌስቡክ)



=========================================
በመጀመሪያ እና በመጨረሻ

በመጀመሪያ – አግቡ እንጂ። ልጅም በልጅነት
ሲሆን ነው የሚያምረው።
ከዚያ – ውለዱ እንጂ። ቤት ያለ ልጅ አይሞቅም።
ከዚያ – ሲወለድ ድገሙ እንጂ። አብረው ያድጋሉ።
ከዚያ – አንድ ሲወለድ፣ ለሴቷ እህት
ያስፈልጋታል።
ከዚያ – ወንድ ከተወለደ፣ ግድ የለም ድገሙ ፈጣሪ
ያውቃል።
ከዚያ – አሁንም ወንድ ከሆነ፣አንድ ሞክሩና ካልሆነ
ይቀራል።
ከዚያ – አምስት ሲሆኑ ግን በዚህ የኑሮ ውድነት
አምስት ልጅ አልበዛም? (በሹክሹክታ) እንግዲህ
ገቢያቸውን የሚያውቁት እነሱ ናቸው።
በመጨረሻም – ሳይቸግራቸው ቀፍቅፈው
ቀፍቅፈው ይኸው ማጣፊያው አጠራቸው። ለስሙ
ተምረው የለም? እንግዲህ ከመምከር አልፈን አልጋ
ልንለያቸው አንችልም። እኛ የማንወልደው ልጅ
ጠልተን ነው? ፈጥሮ በሰው ነፍስ መጫወት!
(ከቴዎድሮስ ተ/አረጋይ ፌስቡክ)

Read 10627 times