በፖሊስ መኮንንነትና በመረጃ ባለሙያነት ሀገራቸውን ያገለገሉትሌተና ኮሎኔል ተፈራ ካሳ “ዘፍ
ያለው” በሚል ርዕስ ያዘጋጁት መፅሃፍ ለገበያ ቀርቧል። ኮለኔሉ በ20 ዓመት አገልግሎታቸው የአይን እማኝ የሆኑበትን የኢትዮ ሶማሌ ጉዳይ እንዲሁም በወቅቱ የነበረውን የአገራችን አጠቃላይ ፖለቲካ ትኩሳት በመረጃ አስደግፈው በትረካ መልክ ያቀረቡበት ይሄው መፅሀፍ
የስለላና የአፈና ትንቅንቅን የሚያስቃኝ እውነተኛ ታሪክ ሲሆን በሁለተኛው ‹‹ለንባብ ለህይወት›› የመፅሀፍት አውደርዕይ መክፈቻ ላይ በድምቀት ተመርቋል፡፡ሌተናል ኮሎኔሉ መፅሐፉን ፅፈው ለህትመት ያዘጋጁት በ1985 ዓ.ም ቢሆንም በተለያዩ ምክንያቶች የህትመት ብርሀን ሳያገኝ እንደቆየ የተገለፀ ሲሆን እርሳቸው ካለፉ በኋላ ልጃቸው ቴዎድሮስ ተፈራ መፅሐፉን የበለጠ በአርትኦት አበልፅጎ ለንባብ እንዳበቃው ለአዲስ አድማስ ገልጿል፡፡ ሌተናል ኮሎኔሉ 12 ዓመት በፖሊስ ሰራዊት ውስጥ በአስተዳደር፣ በወንጀል ምርመራ በቴክኒክ ክፍል ስምንት ዓመት
ደግሞ በፀጥታ ጥበቃ መስሪያ ቤት የመረጃ ሀላፊዎች የቅርብ ረዳት ሆነው ባገለገሉበት ወቅት በአይናቸው ያዩዋቸው የተሳተፉባቸው እውነተኛ ክንውኖች በመፅሀፉ ተካተዋል መፅሀፉ በ341 ገፅ ተመጥኖ በ150 ብር እና በ25 የአሜሪካ ዶላር ለገበያ ቀርቧል፡፡
Latest from Administrator
- የእስራኤል እና የኢራን ፍጥጫ
- Insights on Israel's Response: Interview with Mr. Tomer Bar-Lavi, Chargé d’Affaires at the Embassy of Israel to Ethiopia
- Barr, a vocal Trump critic, says he will ‘support the Republican ticket’ in November
- Iran president warns of ‘massive’ response if Israel launches ‘tiniest invasion’
- "አልሞቷል" ፊልም ዛሬ በዓለም ሲኒማ ይመረቃል