ምርቃቱን አስመልክቶ ለአዲስ አድማስ ማብራሪያ የሰጠው የሲኒማ ቤቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ታምራት አበበ ሲኒማ ቤቱ ለአካባቢው ሕዝብ የተሻለ የመዝናኛ እድል መክፈቱን ገልፆ ከሦስት ወር በፊት ተከፍቶ ሥራ ሲጀመር ከፊልም ፕሮዲዩሰሮች ጋር ባለመላመድ የተነሳ ችግሮች መኖራቸውንና አሁን ግን ለውጥ መኖሩን ተናግሯል፡፡ 350 ወንበሮች ያሉት ሲኒማ ሴፍ የሚያሳየው የአማርኛና ሌሎች የሀገር ውስጥ ቋንቋዎችን ፊልሞችን ብቻ ነው፡፡