Monday, 05 March 2012 13:50

“ቦምቡ ፍቅርሽ” ትያትር እና “የሴቶች ጉዳይ” ፊልም መረቃሉ “ያመለጠው እስረኛ” ትያትር ተመረቀ

Written by  መልካሙ ተክሌ (melkamutekele@gmail.com)
Rate this item
(0 votes)

በአሜሪካዊው ሳም ሼፓርድ የተፃፈውና በለዓለም ብርሃኑ ተተርጉሞ የተዘጋጀው “ቦምቡ ፍቅርሽ” የተሰኘ የኮሜዲ ትያትር የፊታችን ማክሰኞ በሀገር ፍቅር ትያትር ቤት ይመረቃል፡፡ ትያትሩን ፕሮዲዩስ ያደረገው ጂ አዲ የኪነጥበብ ፕሮሞሽንና ቴአትር ኢንተርፕራይዝ ነው፡፡ በትያትሩ ሞገስ ወልደ ዮሃንስ፣ ዕታገኝ መልካ፣ ተስፋዬ ማሞ፣ መስፍን ጋሻው እና ረታ ወርቁ ተውነዋል፡፡

በቾምቤ ፕሮዳክሽን የቀረበው “ያመለጠው እስረኛ” የተሰኘው ልብ ሰቃይ ቴአትር ባለፈው ማክሰኞ በአዲስ አበባ ማዘጋጃ ቤት ትያትር እና ባህል አዳራሽ ተመረቀ፡፡ ስዩም ተፈራ ጽፎ ባዘጋጀው ቴአትር ላይ አበባው መላኩ፣ መስፍን አይፎክሩ፣ ማክዳ ኃይሌ፣ ሙሉነሽ ተሰማ፣ ፍፁም ተሾመ እና ግዛቸው መኩሪያ ይተውናሉ፡፡

አልመንሱር ፊልም ፕሮዳክሽን ከኢንስታሌሽን ፊልም ፕሮዳክሽን ጋር በመሆን ያቀረቡትና የደራሲና አዘጋጅ መቅደስ በቀለ (ማክዳ) “የሴቶች ጉዳይ” ፊልም ማክሰኞ ይመረቃል፡፡

የ105 ደቂቃ ርዝመት ባለው አስቂኝ የፍቅር ፊልሙ ላይ ሳምሶን ታደሰ (ቤቢ)፣ ህሊና ሲሳይ፣ ዮናስ አሰፋ፣ እስማኤል ኢብራሂም እና ሌሎችም ተውነዋል፡፡ የፊልሙ ዝግጅት ዘጠኝ ወራት ፈጅቷል፡፡

 

 

Read 1478 times Last modified on Monday, 05 March 2012 13:53