Print this page
Monday, 08 August 2016 06:04

የአመቱ የዓለማችን ሃብታም ደራሲያን ይፋ ተደረጉ

Written by 
Rate this item
(6 votes)

ደራሲ ጄምስ ፓተርሰን በ95 ሚ. ዶላር ቀዳሚነቱን ይዟል
    ታዋቂው ፎርብስ መጽሄት፤በድርሰት ስራዎቻቸው ከፍተኛ ገቢ ያገኙ የአመቱ የዓለማችን እጅግ ሃብታም ደራሲያንን ዝርዝር በሳምንቱ መጀመሪያ ላይ ይፋ ያደረገ ሲሆን ባለፉት 12 ወራት ብቻ 95 ሚሊዮን ዶላር ገቢ ያገኘው ታዋቂው ደራሲ ጄምስ ፓተርሰን በአንደኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል፡፡ በወንጀል ነክ ድርሰቶቹ የሚታወቀው ጄምስ ፓተርሰን፤ ባለፉት ሶስት አመታት በፎርብስ የሃብታም ደራሲያን ዝርዝር ውስጥ ቀዳሚነቱን ይዞ መዝለቁን የጠቆመው መጽሄቱ፤ይሄው ደራሲ በቀጣዩ አመትም ክብሩን እንደጠበቀ ይዘልቃል ተብሎ እንደሚገመት አስታውቋል፡፡
በ2016 የአለማችን ሃብታም ደራሲያን ዝርዝር ውስጥ ሁለተኛ ደረጃን የያዘው 19.5 ሚሊዮን ዶላር ያገኘው የህጻናት መጽሃፍት ደራሲው ጄፍ ኬኒ ሲሆን  ሃሪ ፖተር በሚለው ተከታታይ መጽሃፏ አለማቀፍ ዝናን ያተረፈቺው ጄ ኬ ሮውሊንግ ደግሞ በ19 ሚሊዮን ዶላር ሶስተኛ ደረጃን ይዛለች፡፡ ጆን ግሪሻም በ18 ሚሊዮን ዶላር አራተኛ፣ ስቴፈን ኪንግ፣ ዳንኤላ ስቲልና ኖራ ሮበርትስ ደግሞ በተመሳሳይ በ15 ሚሊዮን ዶላር አመታዊ ገቢ አምስተኛ ደረጃን ይዘዋል፡፡ በዝርዝሩ ውስጥ ከተካተቱት ሌሎች ደራሲያን መካከልም ጆን ግሪን፣ ዳን ብራውንና ቬሮኒካ ሮዝ ይገኙበታል ተብሏል፡፡
የተለያዩ የአለማችን አገራትን ደራሲያን አመታዊ የመጽሃፍ ሽያጭና ገቢ በማስላት የላቀ ገቢ ያገኙ ደራሲያንን ዝርዝር ይፋ የሚያደርገው ፎርብስ መጽሄት፤ባለፉት 12 ወራት ከፍተኛ ገቢ ያገኙ በሚል በዝርዝሩ ያካተታቸው 14 የተለያዩ የአለማችን አገራት ደራሲያን በድምሩ 269 ሚሊዮን ዶላር ማግኘታቸውን አስታውቋል፡፡

Read 2854 times
Administrator

Latest from Administrator