Monday, 15 August 2016 09:17

ቻይናዊው “ከሞትክ 10 አመታት አልፎሃል” ተባለ

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

ስራ ለመቀጠር የሚያስችለውን ከወንጀል ነጻ መሆኑን የሚያረጋግጥ ማስረጃ እንዲሰጠው ለመጠየቅ ወደ አንድ የአገሪቱ ፖሊስ ጣቢያ ያመራው ቻይናዊ÷ ከፖሊስ መኮንኖች “ምን ማለትህ ነው!?... አንተ እኮ ወንጀል ሰርተህ በመገኘትህ ከአስር አመታት በፊት በስቅላት የተገደልክ ሰው ነህ!... ሞተሃል!...” የሚል ምላሽ ተሰጠው ይላል ቢቢሲ፡፡
ቼን የተባለው የ45 አመት ቻይናዊ፣ በ2006 በፈጸመው ወንጀል ጥፋተኛ ሆኖ በመገኘቱ በፍርድ ቤት በተሰጠ ውሳኔ በስቅላት እንደተገደለ የሚያረጋግጥ መረጃ እንዳገኙ በፖሊሶች እንደተነገረው የጠቆመው ዘገባው፤ ግለሰቡ ግን “እመኑኝ ወንጀል አልሰራሁም፣ በስቅላትም አልተገደልኩም፣ በህይወት አለሁ” ሲል አቤቱታ ማቅረቡን ገልጧል፡፡
የግለሰቡን የአልሞትኩም እመኑኝ አቤቱታ ተቀብሎ ሲመረምር የሰነበተው የዡሃንግዙ ፖሊስም፣ ጉዳዩ በስህተት የተፈጸመ እንደሆነና በተባለው ወንጀል የስቅላት ሞት የተፈረደበትና የተገደለው ሰው ሌላ ስመ ሞክሼ እንደሆነ መረጋገጡን አስታውቋል ብሏል ዘገባው፡፡
ወንጀል ሰርቶ በመገኘቱ ከአስር አመታት በፊት በስቅላት የተገደለው ትክክለኛው ቼን፣ ከዚህኛው ቼን ጋር ተመሳሳይ ስምና የነዋሪነት መታወቂያ ቁጥር እንዳለው መረጋገጡን ያስታወቀው ዘገባው፤በቻይና አንድ አይነት ስም ያላቸውና በስህተት አንድ ዓይነት የመታወቂያ ቁጥር የሚሰጣቸው ሰዎች በተደጋጋሚ ተመሳሳይ ችግር እንደሚገጥማቸውም አክሎ ገልጧል፡፡





Read 1122 times