Sunday, 21 August 2016 00:00

ቱርክ እስር ቤት ስለጠበባት 38 ሺህ እስረኞችን ልትፈታ ነው

Written by 
Rate this item
(3 votes)

   በቅርቡ ከተቃጣበት የመፈንቅለ መንግስት ሙከራ ጋር በተያያዘ ከ26 ሺህ በላይ ዜጎችን ያሰረው የቱርክ መንግስት፣ ባጋጠመው የእስር ቤቶች መጨናነቅ ሳቢያ፣ ከመፈንቅለ መንግስቱ ጋር ባልተያያዙ ወንጀሎች የታሰሩ ነባር 38 ሺህ ያህል እስረኞችን ሰሞኑን እንደሚፈታ ማስታወቁን ሮይተርስ ዘገበ፡፡
ፕሬዚዳንት ጣይብ ኤርዶጋንን ከስልጣን ለማስወገድ የተካሄደው የመፈንቅለ መንግስት ሙከራ መክሸፉን ተከትሎ የአገሪቱ ፖሊስ በርካታ ቁጥር ያላቸውን ዜጎቹን እያፈሰ ወደ እስር ቤቶች ማጋዙ በእስር ቤቶች ላይ ከፍተኛ መጨናነቅ መፍጠሩን የጠቆመው ዘገባው፤የአገሪቱ የፍትህ ሚኒስትር በኪር ቦዝዳግ፣ ችግሩን ለመፍታት በማሰብ 38 ሺህ እስረኞችን ለመፍታት መወሰናቸውን እንዳስታወቁ ገልጧል፡፡በተለያዩ የወንጀል ክሶች ተጠርጥረው የታሰሩት እነዚህ 38 ሺህ እስረኞች ከእስር ይለቀቁ እንጂ ምህረት አልተደረገላቸውም ያሉት ሚኒስትሩ፤ ጉዳያቸው በፍርድ ቤት ተመርምሮ ተገቢው ቅጣት እንደሚጣልባቸው ማስታወቃቸውን ዘገባው አስረድቷል፡፡

Read 2749 times