Sunday, 21 August 2016 00:00

“የብርሃን ፍቅር” የፊታችን ሰኞ ይመረቃል

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

የታላቁ ገጣሚና ፀሐፌ-ተውኔት ደበበ ሠይፉን ‹‹የብርሃን ፍቅር (ለራስ የተፃፈ ደብዳቤ )›› በድጋሚ ማሳተሙን የገለጸው ሐሳብ አሳታሚ፤ከነገ ወዲያ ሰኞ በ10፡30 በተለያዩ የጥበብ መሰናዶ በቅርስ ጥናትና ጥበቃ ባለሥልጣን አዳራሽ ያስመርቃል፡፡ በምርቃት ሥነስርዓቱ ላይ ደራሲና ሃያሲ አለማየሁ ገላጋይ በደበበ ሠይፉ ስራዎች ላይ ዳሰሳዊ ቅኝት የሚያቀርብ ሲሆን በአዲስ አድማስ ጋዜጣ ላይ በሚከትባቸው ጥበባዊ ጽሁፎቹ የሚታወቀው ተፈሪ መኮንን፣ ስለ ደበበ ሠይፉ መምህርነት፤ ተዋናይ ተፈሪ አለሙ፣ ስለ ፀሐፌ-ተውኔት ደበበ ሠይፉ፤እንዲሁም ገጣሚ ታገል ሰይፉ ስለ ደበበ ሠይፉ አንዳንድ ትዝታዎች እንደሚያወጉ ታውቋል። አንጋፋና ወጣት ገጣሚያንም ስራዎቻቸውን ለታዳሚው ያቀርባሉ፡፡ የሥነጽሁፍ ወዳጆች በምርቃት ሥነስርዓቱ ላይ እንዲገኙ ሐሳብ አሳታሚ ጋብዟል፡፡  

Read 2433 times