Sunday, 21 August 2016 00:00

ሃሳብዎን በ“ነፃነት” ይግለጹ!!

Written by 
Rate this item
(2 votes)

1- ለተቃውሞ አደባባይ በተወጣ ቁጥር ግጭቶች
እየተከሰቱ፣የዜጎች ህይወት እንዳይጠፋና ንብረት
እንዳይወድም ምን ይደረግ ይላሉ?
ሀ) ህገ-መንግስቱን አክብሮ ማስከበር!
ለ) የዳበረ የዲሞክራሲ ባህል ካላቸው አገራት ልምድ
መውሰድ!
ሐ) ለሰዎች ህይወት ትልቅ ዋጋ መስጠት!
መ) ተቃውሞውንም ምላሹንም ሰላማዊ ማድረግ!
ሠ) ጥይት ከመተኮስ፤አስለቃሽ ጭስ መተኮስ!
2- የጎንደር ነዋሪዎች ሰሞኑን ለ3 ቀናት ሰላማዊ የቤት
ውስጥ አድማ አድርገዋል፡፡ ብዙዎች በትብብራቸውና
በጽናታቸው ተደንቀዋል፡፡ እርስዎስ ምን አሉ?
ሀ) ቁጥር 1 አድናቂያቸው ነኝ!!
ለ) አድማው ህይወትና ወጪ ቆጣቢ ነው!!
ሐ) ትብብሩ ለተቃውሞ ብቻ ሳይሆን ለዕድገትም
ይቀጥል!
መ) ህዝባዊ ተቃውሞን ሳያዘምኑት አይቀርም!
ሠ) የጸጥታ ሃይሉ ቤት ልግባ አለማለቱ!
3. የፌደራል ሥርዓቱ ለአንድነታችን አደጋ ነው ወይስ
ዋስትና ነው?
ሀ) እያየነው፤ከባድ አደጋ ነው እንጂ!
ለ) አደጋም ዋስትናም አይሆንም!
ሐ) እንደ አገር የምንቀጥለው በፌዴራል ሥርዓቱ
ብቻ ነው!
መ) ለአንድነታችን አደጋም ዋስትናም እኛው ነን!
ሠ) ኢትዮጵያዊነት ዳግም ያንሰራራል!
4. በየአካባቢው የሚከሰቱ ህዝባዊ ተቃውሞዎች
በእርግጥ መንግስት እንደሚለው፣በውጭ ሐይሎች
የሚመሩ ናቸው ብለው ያምናሉ?
ሀ) ሰላማዊ ተቃዋሚዎችን የሚገድሉት የውጭ
ሃይሎች እንዳይሆኑ!
ለ) የሰለቸ ፕሮፓጋንዳ ነው!
ለ) አሁንም መንግስት የነቃ አይመስልም!
ሐ) የእኔ ማመን አለማመን ለውጥ አያመጣም!
ሠ) መንግስት ወደ ውጭ ከሚጠቁም ቤቱን ያጽዳ?!
5. በቅርቡ በኦሮሚያና በአማራ ክልሎች የተነሱ ህዝባዊ
ተቃውሞዎችን ተከትሎ በተከሰቱ ግጭቶች በጸጥታ
ሃይሎች የተገደሉ ዜጎችን ቁጥር የሚያጣራ ታዛቢ ቡድን
ለመላክ ተመድ ጥያቄ ቢያቀርብም መንግስት ውድቅ
አድርጎታል፡፡ የመንግስት ውሳኔ ተገቢ ነው ይላሉ?
ሀ) አይደለም ብል ምን አመጣለሁ!
ለ) ራሱ አጣርቶ ተመጣጣኝ እርምጃ ነው ይለናል!
ሐ) እንኳን ተመድን ህዝብንስ መች ተቀበለ!
መ) መንግስት አዛዥ ናዛዥ ሆኗል!
ሠ) አልልም!
(N.B- ከተሰጡት ምርጫዎች ውስጥ ለእርስዎ
የሚስማማ ከሌለ፣
የራስዎትን ምርጫ (ረ) የማካተት መብትዎ የተጠበቀ
ነው!!!)

Read 1222 times