Sunday, 04 September 2016 00:00

አፕል 14.5 ቢ. ዶላር ያልተከፈለ ግብር እንዲከፍል ተወሰነበት

Written by 
Rate this item
(0 votes)

ታዋቂው የቴክኖሎጂ ምርቶች አምራች ኩባንያ አፕል፤ በአየርላንድ በሚያደርገው የንግድ እንቅስቃሴ በህገ-ወጥ መንገድ ሳይከፍለው የቀረውን የ14.5 ቢ ዶላር የግብር ዕዳ እንዲከፍል በአውሮፓ ህብረት አጣሪ ቡድን እንደተወሰነበት ስካይ ኒውስ ዘገበ፡፡
ህብረቱ ለ3 አመታት ከዘለቀ ምርመራ በኋላ በኩባንያው ላይ ይህንን ክብረ ወሰን ያስመዘገበ የተባለ የግብር ቅጣት የጣለው አየርላንድ ለኩባንያው ያልተገባ የግብር ጥቅማ ጥቅሞችን በህገ ወጥ መንገድ መስጠቷን በማረጋገጡ ነው ተብሏል። አፕልና የአየርላንድ መንግስት ህብረቱ ያሳለፈውን ውሳኔ በመቃወም ይግባኝ እንደሚጠይቁ የገለጹ ሲሆን፣ ውሳኔው የኩባንያዎቼን ስኬት ለማደናቀፍ እየሰራ ነው ስትል ህብረቱን ስትከስ የቆየቺውን አሜሪካን ክፉኛ ያስቆጣል ብሏል - ዘገባው፡፡
 አየርላንድ የአሜሪካ ኩባንያዎች በስፋት ተሰማርተው ትርፋማ ለመሆን የሚያስችል ስራ እንዲሰሩ የከፈተቺው እድል ለውዝግቡ መነሻ እንደሆነ ዘገባው አስታውሷል፡፡

Read 930 times