እናት የማስታወቂያ ድርጅት ከጎተ የባህል ማዕከልና ከብሄራዊ ቤተ- መፃህፍትና ቤተ-መዛግብት ኤጀንሲ ጋር በመተባበር በበእውቀቱ ስዩም ‹‹ከአሜን ባሻገር›› የተሰኘ ታሪክ ቀመስ መፅሀፍ ላይ ነገ ከቀኑ 8፡00 ጀምሮ በወመዘክር ውይይት ያካሂዳል፡፡ ለውይይቱ የመነሻ ሀሳብ የሚያቀርቡት በአ.አ.ዩ በፎክሎር የትምህርት ዘርፍ እጩ የዶክትሬት (PhD) ተመራቂ የሆኑት አቶ ገዛኸኝ ፀጋው ሲሆኑ ፍላጎት ያለው በውይይቱ ላይ እንዲሳተፍ እናት የማስታወቂያ ድርጅት ጋብዟል፡፡
Saturday, 03 September 2016 12:05
‹‹ከአሜን ባሻገር›› ላይ ነገ ውይይት ይካሄዳል
Written by ናፍቆት ዮሴፍ
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና