Saturday, 10 September 2016 15:24

የህንዱ ባለጸጋ ለ1 ቢ. ዜጎች የ4ጂ ኢንተርኔት በነጻ አቀረቡ

Written by 
Rate this item
(4 votes)

በአገረ ህንድ ቁጥር አንድ ባለጸጋ የሆኑት ህንዳዊው ቢሊየነር ሙኬሽ አምባኒ ለ1 ቢሊዮን ያህል የአገሪቱ ዜጎች ያለምንም ክፍያ መጠቀም የሚችሉበትን እጅግ ፈጣን የሆነ የ4ጂ ኢንተርኔት አገልግሎት ማቅረባቸውን ሲኤንኤን ዘገበ፡፡ ቢሊየነሩ ያቋቋሙትና ሪሊያንስ ጂኦ የተሰኘው የኢንተርኔት አገልግሎት፤ከአገሪቱ 80 በመቶ ያህሉን አካባቢ የሚሸፍን ሲሆን ህንዳውያን ይህን እጅግ ፈጣን ገመድ አልባ የኢንተርኔት አገልግሎት እስከ 2016 መጨረሻ ያለ ምንም ክፍያ መጠቀም ይችላሉ ተብሏል፡፡
ተጠቃሚዎች የነጻ አገልግሎቱ የጊዜ ገደብ ካለፈ በኋላም እጅግ ርካሽ በሆነ ክፍያ ተጠቃሚ የሚሆኑበትን እድል የፈጠሩት ባለሃብቱ፣ ለዚህ አገልግሎት የሚከፍሉት 2.5 ዶላር ወርሃዊ ክፍያ ብቻ መሆኑን አስታውቀዋል፡፡ የባለሃብቱ የኢንተርኔት አገልግሎት እጅግ ፈጣን እንደሆነ የተነገረ ሲሆን፣ በሰከንድ 21 ሜጋ ባይት ፍጥነት እንዳለው ተጠቁሟል፡፡
ታዋቂው ፎርብስ መጽሄት እንዳስነበበው፤የነዳጅ ኩባንያዎችና የታላላቅ የንግድ ተቋማት ባለቤት የሆኑት ህንዳዊው ቢሊየነር ሙኬሽ አምባኒ፣ በዚህ አመት የዓለማችን ቢሊየነሮች ዝርዝር ውስጥ 36ኛ ደረጃን የያዙ ሲሆን፣ ግለሰቡ የተጣራ 22 ቢሊዮን ዶላር ሃብት አላቸው፡፡

Read 1415 times