ሚዩዚክ ሜይዴይ፤ ከኢትዮጲስ ኮሌጅ ጋር በመተባበር፣ ነገ ከቀኑ 8፡00 ጀምሮ በብሄራዊ ቤተ-መፃህፍትና ቤተ መዛግብት ኤጀንሲ አዳራሽ፣ ‹‹ምስክርነት›› በተሰኘው የሻምበል ተስፋዬ ርስቴ መፅሐፍ ላይ ውይይት ያካሂዳል፡፡ ለውይይቱ የመነሻ ሀሳብ የሚያቀርቡት የ‹‹ጅቡቲ›› መፅሐፍ ደራሲ የሆኑት ዶ/ር በለጠ በላቸው ሲሆኑ፣ማንኛውም ፍላጎት ያለው ሰው በውይይቱ ላይ እንዲሳተፍ ሚዩዚክ ሜይዴይ ጋብዟል፡፡
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና