Sunday, 18 September 2016 00:00

‹‹መስቀልና ባህላዊ አከባበሩ›› የመዝናኛ ፕሮግራም ይካሄዳል

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

 አብርሀም ግዛው ኢንተርቴይመንትና የፕሬስ ስራዎች፣ ከጄቲቪ ጋር በመተባበር ‹‹መስቀልና ባህላዊ አከባበሩ›› የተሰኘ ልዩ የመዝናኛ ፕሮግራም ማዘጋጀቱን ገለጸ፡፡
ፕሮግራሙ በካፒታል ሆቴል ነገ የሚቀረጽ ሲሆን የአገር ሽማግሌዎች ምርቃት፣ የእርድ ስነ-ስርዓት፣ የደመራ ማብራት ስነ- ስርዓት፣ ባህላዊና ዘመናዊ የሙዚቃ ዝግጅቶች፣ ባህላዊ የጉራጌ አለባበስ የፋሺን ትርኢትና ሌሎች ዝግጅቶች እንደሚካሄዱ ለማወቅ ተችሏል፡፡ በፕሮግራሙ ላይ ታዋቂ ሰዎች ገጠመኞቻቸውን ለታዳሚው የሚያካፍሉ ሲሆን በጉራጌ ማህበረሰብ ለመስቀል በዓል የሚደረገው ቅድመ ዝግጅት ለዕይታ ይቀርባል ተብሏል፡፡ በመዝናኛ ፕሮግራሙ ላይ ታዋቂ ሰዎች፣ አርቲስቶች፣ የሚዲያ ባለሙያዎችና ጥሪ የተደረገላቸው የመንግስት የስራ ሃላፊዎች እንደሚታደሙ አዘጋጁ ጋዜጠኛ አብርሃም ግዛው ጨምሮ ገልጿል፡

Read 783 times