በምግብ ዝግጅት ባለሙያዋ አዝመራ ካሳሁን የተፃፈውና ከ6 ወር ህፃን፣ ት/ቤት እስከ ሚቋጠር የልጆች ምግብ አዘገጃጀት ያስተምራል የተባለው “ከቤት እስከ ት/ቤት” የተሰኘ የህፃናት ምግብ አዘገጃጀት መፅሐፍ ዛሬ በካሌብ ሆቴል ከረፋዱ 4፡00 ጀምሮ ይመረቃል፡፡
በ51 ገፆች የተቀነበበውና በ50 ብር ለገበያ የቀረበው መፅሀፉ፤ የትኛውም ወላጅ በአካባቢው በቀላሉ በሚገኙ የምግብ ጥሬ ዕቃዎች ለልጆቹ እንዴትና በምን ሁኔታ ምግብ በማዘጋጀት መመገብና ጤናማ ማድረግ እንደሚችል ያሳያል ተብሏል፡፡በምርቃት ስነ - ስርዓቱ ላይ ወላጆች፣ የት/ቤቶች ባለቤቶች ህፃናት ላይ የሚሰሩ ድርጅቶችና በርካታ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች እንደሚገኙ የመፅሀፉ አዘጋጅ ወ/ሮ አዝመራ ካሳሁን ተናግረዋል፡፡
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና