Monday, 19 September 2016 08:25

ኦርቴጋ ረቡዕ እና ሐሙስ የአለማችን ቁጥር 1 ቢሊየነር ሆነው ነበር

Written by 
Rate this item
(4 votes)

    ስፔናዊው ቢሊየነር አማኒኮ ኦርቴጋ፤ባለፈው ሳምንት ረቡዕ እና ሃሙስ የማይክሮሶፍቱን መስራች ቢል ጌትስን በመብለጥ ለሁለት ቀናት ብቻ የአለማችን ቁጥር አንድ ቢሊየነር ሆነው እንደነበር ፎርብስ መጽሄት ዘግቧል፡፡ ታ
ዋቂውን ዛራ ጨምሮ የኦርቴጋ ኩባንያዎች ረቡዕ ዕለት የ2.5 በመቶ የአክስዮን ድርሻ ጭማሪ ማሳየታቸውን ተከትሎ፣ የቢሊየነሩ የሃብት መጠን በ1.7 ቢሊዮን ዶላር በማደግ 77.8 ቢሊዮን ዶላር መድረሱንና በዚህም ግለሰቡ የቤል ጌትስን ቦታ በመረከብ የአለማችን ቁጥር አንድ ቢሊየነር መሆን መቻላቸውን ዘገባው ገልጧል፡፡
አርብ ዕለት ማለዳ ግን፣ የእኒሁ ቢሊየነር ኩባንያዎች የአክስዮን ድርሻ በ2.8 በመቶ በመቀነሱ፣ ኦርቴጋ የአለማችን ቀዳሚ ቢሊየነርነቱን ስፍራ ለቢል ጌትስ በማስረከብ ወደ ሁለተኛ ደረጃቸው ተመልሰዋል ተብሏል፡፡
ኦርቴጋ ለመጀመሪያ ጊዜ የአለማችን ቁጥር አንድ ቢሊየነር ለመሆን የቻሉት ባለፈው የፈረንጆች አመት 2015 ጥቅምት ወር ላይ እንደነበር ያስታወሰው ዘገባው፣ በወቅቱ የተጣራ ሃብታቸው 80 ቢሊዮን ዶላር እንደነበርም ጠቅሷል፡፡

Read 3787 times