Sunday, 25 September 2016 00:00

‹‹መንገድ›› የግጥም መድበል ገበያ ላይ ዋለ

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

   የገጣሚ ሄኖክ ስጦታው ሶስተኛ ስራ የሆነውና ‹‹መንገድ›› የተሰኘው የግጥም መድበል ገበያ ላይ ዋለ፡፡ ገጣሚው የተለያዩ የህይወት ፍልስፍናዎቹን ያሳየባቸው 64 ያህል ግጥሞች የተካተቱ ሲሆን በመፅሀፉ ጀርባ ‹‹ጠፈጠፍ›› በሚል ርዕስ ገጣሚ አበባ ብርሃኑ በማህበራዊ ጉዳይ ላይ የሚያጠነጥኑ ግጥሞቿን በጋራ አሳትማለች፡፡ በመቶ ገፅ የተቀነበበው መፅሀፉ፤ ለአገር ውስጥ በ49 ብር ከ60 ሳንቲም፣ ለውጭ አገራት በ15 ዶላር ለገበያ የቀረበ ሲሆን አከፋፋዩ ጃፋር መፅሐፍት መደብር ነው፡፡ ገጣሚ ሄኖክ ስጦታው በ1994 ዓ.ም ‹‹ነቁጥ››፣ በ2005 ዓ.ም ደግሞ ‹‹ሀ-ሞት›› የተሰኙ የግጥም መጽሐፍትን ለንባብ ማብቃቱ ይታወሳል፡፡

Read 1931 times