ድምፃዊ ሙሉቀን ዳዊት፣ ቃቆ ጌታቸውና ብስራት ሱራፌል በጋራ ያቀነቀኑበት ‹‹መንገደኛ›› የተሰኘ አዲስ የሙዚቃ አልበም ለአድማጭ ቀረበ፡፡ ግጥምና ዜማው በዓለማየሁ ደመቀ፣ በሙሉቀን ዳዊት፣ በጃሉድና በብስራት ሱራፌል የተሰራ ሲሆን ሙዚቃውን ያቀናበረው ካሙዙ ካሳ ነው ተብሏል፡፡ ‹‹መንገደኛ››ን ጨምሮ 13 ዘፈኖች በአልበሙ መካተታቸውም ታውቋል፡፡ በፍቅርና በማህበራዊ ጉዳይ ላይ የሚያጠነጥኑ ዘፈኖች የሚቀነቀኑበት ይኸው አልበም፤ ቴክሼል የተሰኘ ድርጅት ፕሮዱዩስ ያደረገው ሲሆን ቮካል ሪከርድስ እያከፋፈለው እንደሚገኝ ድምፃዊያኑ ለአዲስ አድማስ ገልፀዋል፡፡
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና